ዜና

ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ

ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል። ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል። ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው። በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው…
Read More
በ947 ምርጫ ጣቢያዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት በፊት ድምጽ መሰጠት መጀመሩ ተገለጸ

በ947 ምርጫ ጣቢያዎች ከጠዋቱ 12 ሰዓት በፊት ድምጽ መሰጠት መጀመሩ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት እንደገለጸው ምልከታ ካደረገባቸው 2 ሺህ 258 ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በ947 ወይም 42 በመቶዎቹ ላይ ከንጋቱ 12 ሰዓት በፊት ድምጽ መሰጠት መጀመሩን ማረጋገጡን ገልጿል፡፡ ድርጅቱ ዛሬ ግንቦት 24፣ 2018 በመካሄድ ላይ ባለው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ምልከታ ባደረገባቸው የምርጫ ጣቢያዎች የተስተዋሉ ክስተቶችን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የኅብረቱ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሳህለሥላሴ አበበ በመግለጫው ላይ እንዳሉት ከትግራይ ክልል ውጪ በቀሪዎቹ ሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተካሄደ ባለው ምርጫ የግማሽ ቀን ምልከታ ሪፖርት ይፋ አድርገዋል፡፡ በዚህም የህብረቱ ታዛቢዎች ከተገኙባቸው 2 ሺህ 258 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ1 ሺህ 276 ወይም 57 በመቶዎቹ ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ…
Read More
ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢ ቡድንን እንዲመሩ ተመረጡ

ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢ ቡድንን እንዲመሩ ተመረጡ

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ 73 አባላትን ያቀፈ የአፍሪካ ኅብረት ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው የኢትዮጵያ ምርጫ 2018 ታዛቢ ልዑካን ቡድን ይመራሉ ተብሏል። በቀድሞው የኬኒያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው፣ የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባቱን ኅብረቱ አስታውቋል። ታዛቢ ቡድኑ ከ37 አገራት የተውጣጡ 73 አባላትን ያቀፈ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ከታዛቢዎቹ ውስጥ 61 በመቶዎቹ ሴቶች እንደሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ቡድን የሚሰማራው ለአጭር ጊዜ ታዛቢነት ሲሆን፣ ጊዜያዊ ጽ/ቤቱን በስካይላይት ሆቴል እንደሚያደርግ አሳውቋል። ታዛቢዎቹ በሁሉም ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደሚሰማሩም ተገልጿል። ሰባተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቴን ጨርሻለሁ ያለው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ ክልል በ8 የምርጫ ክልሎች ሊካሄድ የታሰበው ምርጫ መራዘሙን አስታውቋል። ቦርዱ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት እያደረገ ያለውን ሽግግር ለማጠናከር፣ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን የሚያቀሉ አዳዲስ መመሪያዎችን ይፋ አድርጓል።ባንኩ ባወጣው መግለጫ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን ይበልጥ ለማቅለልና በንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት የሆኑ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶችን የሚያሳጥሩ ናቸው።በአዲሱ መመሪያ መሰረት የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ እና የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ሂሳብ  ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ እና የሰነድ መክፈያ ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል።ይህ ማሻሻያ በተለይ በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ነጋዴዎች የጊዜና የቢሮክራሲ ጫናን ያቀላል ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ያላቸው ተቋማት የባንኮችን ቅድመ ፈቃድ ሳይጠብቁ በሰነድ መክፈያ ስምምነት መሠረት የሸቀጦችን የጭነት ትዕዛዝ መስጠት…
Read More
የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ አነሳ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን የቪዛ ገደብ አነሳ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ ከሁለት ዓመት በኋላ አንስቻለሁ ብሏል፡፡ ህብረቱ በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ሚያዝያ 2016 ወደ አውሮፓ በሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ  አመልካቾች ላይ ገደቦችን ጥሎ እንደነበር ገልጾ ገደቡ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ህብረቱ የቪዛ ገደቦቹን የጣለው በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት የገቡ እና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን የኢትዮጵያ መንግስት ለመመለስ እየተባበረ አይደለም በሚል ምክንያት ነበር፡፡ ከሁለት ወራት በፊት በአዲስ አበባ በተካሄደው የኢትዮጵያ እና አውሮፓ ህብረት የሁለትዮሽ ውይይት ላይ በአውሮፓ ሀገራት የመኖሪያ ፈቃድ ያላገኙ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው ከመመለስ አንጻር የኢትዮጵያ መንግስት ያሳየውን መሻሻል አድንቆ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ከጣላቸው የቪዛ ገደቦች መካከልም የቪዛ ማመልከቻ ጊዜ…
Read More
ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

በግብይት ወቅት ማናቸውም ግብር ከፋይ ነጋዴ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲያከናውን ወይም ዋጋ አሳንሶ የተገኘ በእያንዳንዱ ደረሰኝ የአንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት መጣል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። ያለ ደረሰኝ ሲገበያይ የተገኘ ማንኛውም ግብር ከፋይ ለገዢ ባልሰጠው በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት ከዚህ ቀደም 50 ሺህ ብር ይቀጣ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ማሻሻያ በተደረገለት የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ መሰረት ወደ አንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት ከፍ ብሏል።የገንዘብ ሚኒስቴር እንደ ዋና ማሻሻያዎች ካነሳቸው መካከል የታክስ የምስክር ወረቀት አሰጣጥን ማሻሻል፣ የታክስ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በማስታረቅ ሥርዓት መፍታት፣ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የሚታረምበትን ሥርዓት ግልጽ ማድረግ፣ እንዲሁም የውሳኔ ማስታወቂያ ማሻሻያና የይግባኝ ማቅረቢያ የጊዜ ገደቦችን በግልጽ ማስቀመጥ የሚሉት ይገኙበታል።እነዚህ…
Read More
ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ዜጎቿ ደህንነት እንዲጠበቅ መጠየቋ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ዜጎቿ ደህንነት እንዲጠበቅ መጠየቋ ተገለጸ

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ መጠየቃቸው ተገልጿል። ሚንስትሩ ጌዲዮን ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፣ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከሳዑዲ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋሊድ ኤልክረጂ ጋር በተወያዩበት ወቅት መሆኑን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። ጌዲዮን፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ለኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ እድሎችን እንዲያመቻችም መጠየቃቸውን ሚንስቴሩ ጠቅሷል። ሚንስትር ዋሊድ፣ ሕጋዊ የሠራተኞች ፍልሠት ኢትዮጵያዊያን ደኅንነቱ የተጠበቀ የሥራ ቅጥር እድል እንዲያገኙ ለማስቻል አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል ተብሏል። የሳዑዲ ዓረቢያ ፍርድ ቤት ከአደንዛዥ እጽ ዝውውር ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት የጣለባቸው በርካታ ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በውይይቱ ወቅት ይነሳ አይነሳ መረጃው አላመለከትም። በየ ዓመቱ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ…
Read More
ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት በ10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ  8.71 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር አስታውቋል። በ2018 በጀት ዓመት የ10 ወራት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ከታቀደው ግብ በላይ ውጤት መመዝገቡን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 7.25 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ፣ 8.71 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን አስታውቀዋል። የወጪ ንግድ አፈጻጸም ባለፈው ዓመት (2017 ዓ.ም) ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገበው የ6.08 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ43.32 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ሚንስትሩ አብራርተዋል። ይህ ስኬት በዋናነት በንግድ ዘርፉ ላይ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ውጤት መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመው፤ በላኪዎችና በዘርፉ ተዋንያን መካከል የተፈጠረው…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ አነሳች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ጥላው የነበረውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ አነሳች

በኢትዮጵያ ላይ ተጥሎ የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን አሜሪካ አስታውቃለች። ማዕቀቡ መነሳቱን የገለፀው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአገር መከላከያ ንግድ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ነው። ዳይሬክቶሬቱ፣ በኢትዮጵያ ላይ ይከተል የነበረውን የክልከላ ፖሊሲ በማንሳት አሁን ላይ በዓለም አቀፍ የጦር መሣሪያ ዝውውር ደንብ (ITAR) ቁጥጥር የሚደረግባቸውን እና ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዙ የፈቃድ ማመልከቻዎችን በየተራ እየገመገመ ነው። ይህን ተከትሎ በቅርቡ በሚወጣ የደንብ ለውጥ፣ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጦር መሳሪያ ዝውውር ደንብ - ITAR 126.1 ዝርዝር ውስጥ ከሚገኙ አገራት ተርታ "እንድትሰረዝ" የሚደረግ መሆኑን ጠቅሷል። ይህ ደንብ በአሜሪካ ማዕቀብ ስር የሚገኙ የተወሰኑ አገራት፤ ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለፖሊስ፣ ለደህንነት እና ለሌሎችም የአገር ውስጥ የጸጥታ ኃይሎቻቸው የሚሆኑ የመከላከያ ቁሳቁሶችን እና አገልግሎቶችን ከውጭ…
Read More
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

ተቋሙ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽመዋል ያላቸውን 1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ እርምጃመውሰዱን አስታውቋል።  እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ሲሆን ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስጃለሁ ብሏል፡፡   በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103…
Read More