ዜና

በምስራቅ አርሲ ወረዳዎች ከ450 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምስራቅ አርሲ ወረዳዎች ከ450 በላይ ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ያካሄደውን የምርመራ ግኝት ይፋ ባደረገበት 158ኛ ልዩ መግለጫው፣ ቢያንስ ከ450 በላይ ንጹሃን ዜጎች መገደላቸውን አስታውቋል። ሀገር በቀሉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት 37 ገጾች ባሉት ሪፖርቱ መሠረት፣ በዞኑ በሚገኙ ዘጠኝ ወረዳዎች ውስጥ በታጣቂዎች ማንነትንና ኃይማኖትን መሰረት በማድረግ በተፈጸሙ ጥቃቶች የሰው ህይወት ከማለፉ ባሻገር፣ በርካታ ዜጎች ለአካላዊ ጉዳት፣ ለእገታ እና ለአስገድዶ መሰወር ተዳርገዋል። በተጨማሪም ከ14 ሺህ በላይ ሰዎች ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ በርካታ አብያተ ክርስቲያናትና የግል ንብረቶች መዘረፋቸውንና መውደማቸውን አመልክቷል። ኢሰመጉ ባካሄደው የመስክ ምልከታና መረጃ የማሰባሰብ ስራ፣…
Read More
ኤልጂ ለቃኝው ሻለቃ ዘማች ቤተሰቦች የሙዚቃ ስቱዲዮ ሊገነባ ነው

ኤልጂ ለቃኝው ሻለቃ ዘማች ቤተሰቦች የሙዚቃ ስቱዲዮ ሊገነባ ነው

​የደቡብ ኮሪያው የኤሌክትሮኒክስ ግዙፍ ኩባንያ ኤልጂ (LG)፣ በኮሪያ ጦርነት ወቅት ለተሳተፉት የኢትዮጵያ ቃኝው ሻለቃ ዘማቾች የልጅ ልጆች ለተዋቀረው "ቃኝው ክዋየር"  ዘመናዊ የልምምድ ስቱዲዮ ሊገነባ መሆኑን አስታውቋል። ​ስቱዲዮው በአዲስ አበባ በሚገኘው የኮሪያ አርበኞች መታሰቢያ ህንፃ ውስጥ የሚገነባ ሲሆን፣ የድምፅ መከላከያ ፣ ዘመናዊ የድምፅ ሲስተም እና ዲጂታል የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች እንደሚሟሉለት ተገልጿል። ኤልጂ ይህንን የበጎ አድራጎት ፕሮጀክት የሚያከናውነው ከኮሪያ የሀገር ፍቅርና የአርበኞች ጉዳይ ሚኒስቴር እና "Warm Mind" ከተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው። ​በ2018 የተቋቋመው ይህ የሙዚቃ ቡድን፣ እስካሁን ድረስ ቋሚ የልምምድ ቦታ ባለመኖሩ እና የቴክኖሎጂ ቁሳቁስ እጥረት በነበረበት ሁኔታ የባህል አምባሳደር በመሆን የኢትዮጵያ ባህላዊ ሙዚቃዎችን እና እንደ "አሪራንግ" ያሉ የኮሪያ ታዋቂ…
Read More
ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያዊያን ላይ የሞት ፍርደኞችን በስቅላት እንዳትቀጣ ተጠየቀ

ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያዊያን ላይ የሞት ፍርደኞችን በስቅላት እንዳትቀጣ ተጠየቀ

የአፍሪካ የሰዎችና ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን ላይ የተላለፉ ፍርዶችና የሞት ቅጣቶች እንደገና እንዲታዩ "ሁሉንም መንገዶች" እንዲጠቀምና የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ኢትዮጵያዊያን ደኅንነት ለማስከበር አስፈላጊ "የዲፕሎማቲክ" እና "የቆንስላ" ርምጃዎችን እንዲወስድ ጠይቋል። ተቋሙ ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ በበርካታ ኢትዮጵያዊያን ላይ የተጣለው የሞት ቅጣት በእጅጉ እንዳሳሰበው አስታውቋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ኢትዮጵያዊያኑ "የሕግ ውክልና" እና የፍርድ ቤት "የትርጉም አገልግሎት" እንዲያገኙና ከቤተሰባቸው ጋር እንዲገናኙ ጥረት እንዲያደርግ፤ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፍልሠተኞችን መብት "በሁለትዮሽ ግንኙነቶች" እና በጠንካራ "የቆንስላ ድጋፎች" እንዲያስከብርም ኮሚሽኑ ጠይቋል። ሳውዲ አረቢያ የሞት ፍርድ በስፋት ከሚፈጸምባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን በያዝነው ዓመት ብቻ ቢያንስ 12 ኢትዮጵያዊያን የሞት ፍርድ ተፈጽሞባቸዋል። ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ ድርጅት…
Read More
ፖሊስ ከ40 ሺህ በላይ ዜጎችን በህገወጥ መንገድ ያዘዋወሩ ተጠርጣሪዎች መያዙን ገለጸ

ፖሊስ ከ40 ሺህ በላይ ዜጎችን በህገወጥ መንገድ ያዘዋወሩ ተጠርጣሪዎች መያዙን ገለጸ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ " ከ60 በላይ ስደተኞች ለሞት እና በርካታ ሴቶች ለመደፈር ተጠያቂ ናቸው " ያላቸውን 17 አደገኛ ተጠርጣሪ የሰዎች አዘዋዋሪዎች መያዙን አስታውቋል። ፖሊስ እንደገለጸው፣ በ"መሐመድ ጣሂር አደም (ወርዲ)" የሚመራው ቡድን ሰዎችን ከኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በደላሎች አማካኝነት በመልመል በጂቡቲና በየመን በኩል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያዘዋውር ነበር። እነዚህ አዘዋዋሪዎች ከ40 ሺህ በላይ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ እንዳዘዋወሩ እና ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ እንደሰበሰቡ ተገልጿል። ተጎጂዎች በየመን ውስጥ በመጋዘኖች ታግተው ድብደባ፣ ማሰቃየት እና ሌሎች ኢሰብአዊ ድርጊቶች እንደተፈጸሙባቸው ሲገለጽ፣ ቤተሰቦቻቸውን ገንዘብ እንዲልኩ ለማስገደድ የስቃይ ቪዲዮዎች ይላኩ እንደነበር ተጠቁሟል። በምርመራውም ከ60 በላይ ሰዎች መሞታቸውና በርካታ ሴቶች መደፈራቸው መረጋገጡን ፖሊስ በመግለጫው ላይ…
Read More
ኢትዮጵያ ከማልዴቪስ ጋር የአቪዬሽን ስምምነት ተፈራረመች

ኢትዮጵያ ከማልዴቪስ ጋር የአቪዬሽን ስምምነት ተፈራረመች

ኢትዮጵያና ማልዲቭስ የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ተፈራርመዋል። በኢትዮጵያ እና በማልዲቭስ ሲቪል አቪዬሽን ቦርድ መካከል ከሀምሌ 12-14 2018 በአዲስ አበባ ተካሂዷል። ውይይቱን ተከትሎም የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ አበራ እና የማልዲቭስ ሪፐብሊክ የቱሪዝምና ሲቪል አቪዬሽን ሚኒስትር መሀመድ አሚን የሁለትዮሽ አቪዬሽን ስምምነቱን ተፈራርመዋል። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ አበራ ጋር የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የኢኮኖሚ ሬጉሌሽን ዳይሬክተር አቶ ናርዶስ በድሉ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የስትራቴጂክ አሊያንስ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የኢንተርናሽናል አሊያንስ ዳይሬክተር ተገኝተዋል። ይህ ስምምነት በኢትዮጵያና በማልዲቭስ መካከል ቀጥተኛ የአየር ትስስር እንዲጀመር የሚያስችል ሲሆን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ በአምስተኛ የአየር ነፃነት መብት ተጠቅሞ በማልዲቭስ በኩል ወደ…
Read More
አረብ ኢምሬት የሰዎች ዝውውር ወንጀል ተጠርጣሪዎችን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጠች

አረብ ኢምሬት የሰዎች ዝውውር ወንጀል ተጠርጣሪዎችን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጠች

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ዱባይ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በኢትዮጵያውያን ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ የነበሩ ዳውድ ተፈሪ እና ደስታ ተገኝ የተባሉ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ የማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም 105 ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ዱባይ በመውሰድና ከ188 ሚሊየን ብር በላይ ከተጎጂዎች በመሰብሰብ፣ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲፈጽሙ የቆዩ በመሆናቸው ከዱባይ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ሥር ውለው ለኢትዮጵያ ተላልፈው እንዲሰጡ ተደርጓል ብሏል። ተጠርጣሪዎቹ ዱባይ ተቀምጠው ሀገር ውስጥ ባሉ ተባባሪዎቻቸው አማካኝነት ወጣቶችን በመመልመል ወደ ዱባይ በመላክ፣ በተዘጋጀ የማገቻ ቦታ በማቆየት፣ በተለይ በሴቶች ላይ ጥቃት በማድረስና በማሰቃየት ከፍተኛ ወንጀል ሲፈጽሙ የቆዩ መሆናቸው ተረጋግጧል። ፌደራል ፖሊስም ጉዳዩን ሲያጣራ ቆይቶ…
Read More
ኢትዮጵያ ለ15 ሀገራት ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ እንደማትሰጥ አስታወቀች

ኢትዮጵያ ለ15 ሀገራት ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ እንደማትሰጥ አስታወቀች

የኢትዮጵያ ዜግነት እና ኢምግሬሽን እንዳስታወቀው ከ15 ሀገራት ዜግነት ያላቸው መንገደኞች የመዳረሻ ቪዛ እንደማያገኙ ገልጿል። ከኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶሪያ፣ አፍጋኒስታን፣ ኩባ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ፣ የመን እና የኢራን ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ ወይም ቪዛ ኦን አራይቫል የማይሰጣቸው ሀገራት ናቸው። የኬንያ እና ጅቡቲ ዜጎች ግን ያለ ቪዛ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸዋል ተብሏል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተቋሙን ዓመታዊ አፈጻጸም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ቪዛ መሰጠቱን ተናግረዋል ። ተቋሙ በአንድ ዓመት ውስጥ ከአገልግሎት ፈላጊዎች 42 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡም ተገልጿል። በበጀት ዓመት 7 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሰዎች በአየር መንገዶች እና…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 7ኛ ስብሰባው፣ የተለያዩ የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን አቅርቦ ማጽደቁን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠርና ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ያለመ አዳዲስና ወሳኝ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቋል። ኮሚቴው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መወሰኑንም ገልጿል። እስካሁን ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ ተጥሎ የነበረው የ24 በመቶ ቀጥተኛ የብድር ዕድገት ገደብ ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል። በባንኮች ላይ የብድር ገደብ ውሳኔ ተጥሎ የነበረው ኢኮኖሚው በወለድ ምጣኔ ላይ ወደተመሠረተ የገንዘብ ፖሊሲ ሥርዓት እስኪሸጋገር እንደነበር…
Read More
የሁለተኛ ድግሪ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጀ

የሁለተኛ ድግሪ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጀ

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የከፍተኛ ትምህርት ማስረጃ አሰጣጥንና የደረጃ ግምገማ ሂደትን ለማሻሻል ያስችላል የተባለውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት አድርጓል። ባለስልጣኑ "የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 990/2016" ላይ ማሻሻያ ለማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት ጥሪ አቅርቧል። ተቋሙ እንዳስታወቀው ይህ መመሪያ ያስፈለገው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የትምህርት ማስረጃዎችን የማረጋገጥ ሂደት ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ ለማድረግ በሚል ነው። በተለይም በደረጃ ግምገማ እና በማስረጃ ማረጋገጫ ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ታልሞ መዘጋጀቱም ተገልጿል። ይህ መመሪያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የመንግስትም ሆነ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምረው ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ለተመረቁ…
Read More
የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ነጋዴዎችና ላኪዎች የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ታዳጊ ሀገራትን ተጠቃሚ የሚያደርገውን የንግድ ሥርዓት በተሻለ ሁኔታ ተጠቅመው ወደ ዩኬ ገበያ የመግባት ዕድላቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ ቀረበ። ይህ ጥሪ በአዲስ አበባ በተካሄደው የሥልጠና መድረክ ላይ የተላለፈ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ላኪዎች የዕድሉን፣ የመስፈርቶቹንና የተግባራዊ ሂደቶቹን ግንዛቤ እንዲያሳድጉ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከዩኬ የንግድና ልማት መሥሪያ ቤት፣ ከብሪታንያ ኤምባሲና ከኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ የዩኬ ገበያ ለመግባት የሚያስፈልጉ የጥራት ደረጃዎችና የቁጥጥር መስፈርቶች ተብራርተዋል። አምባሳደር ብሩክ መኮንን እንደገለጹት፣ ቡና፣ የግብርና ምርቶችና ጨርቃጨርቅ በዚህ ሥርዓት ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ የወጪ ንግድ ዘርፎች ናቸው። ሆኖም፣ የቀረጥ ቅናሹ ብቻውን…
Read More