Education

ኢትዮጵያ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ እንዳይሰጥ አገደች

ኢትዮጵያ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ እንዳይሰጥ አገደች

በዩንቨርሲቲዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት እንዳይሰጡ እገዳ ተጥሎባቸዋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ከታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በየትኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተሰጠ እና የሚሰጥ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ዕድገት ተቀባይነት እንደማይኖረው አሳውቋል፡፡ ከጥቅምት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የነበረውንና በትግበራ ወቅት ክፍተት የታየበት "የአካዳሚክ ሠራተኞች የደረጃ ዕድገት መመሪያ" በመሻሻል ላይ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ አስታውሷል፡፡ በዚህም ማሻሻያው ተጠናቆ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከሚላክ ድረስ በሁሉም ተቋማት የፕሮፌሰርነት ዕድገት አሰጣጥ ለጊዜው መታገዱን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ ይሁን እንጂ "አንዳንድ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክልከላውን በመጣስ፣ መመሪያውን ባልተከተለ፣ ግልጽነት በጎደለው፣ ወጥነት በሌለው እና ከትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ ሪፎርሞች ጋር በሚጣረስ መልኩ የፕሮፌሰርነት ዕድገት መስጠት እንደቀጠሉ የትምህርት ሚኒስትር…
Read More
እስከ 6ኛ ክፍል ድረስ ያሉ ተማሪዎችን በውጤታቸው ደረጃ መስጠትን ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ

እስከ 6ኛ ክፍል ድረስ ያሉ ተማሪዎችን በውጤታቸው ደረጃ መስጠትን ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ

በሳሙኤል አባተ ኢትዮጵያ የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅን ለማሻሻል ያለመ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅታለች፡፡ ይህ ረቂ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲጸድቅ በትናንትናው ዕለት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም ይህን ረቂቅ አዋጅ ተጨማሪ ውይይቶች እና ሌሎች ግብዓቶች እንዲታከሉበት በሚል ለዝርዝር እይታ ወደ ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡ ይህ ረቂቅ አዋጅ እንደሚለው ከሆነ ተማሪዎች ስለ ሚማሯቸው ቋንቋዎች፣ ስርዓት ትምህርት ዝግጅት፣ መምህራን ቅጥር፣ ተማሪዎች ምዘና፣ ትምህርት ጥራት ማስጠበቂያ መንገዶች እና ሌሎችንም ጉዳዮች ይዟል፡፡ ቋንቋዎችን አስመልክቶ በረቂቅ አዋጁ ላይ እንደተቀመጠው የአፍ መፍቻ ቋንቋ እንደ ትምህርት አይነትነት እና እንደ ማስተማሪያ ቋንቋነት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ የሚሰጥ ሆኖ እንደ ትምህርት አይነትነት እና እንደ ማስተማሪያ ቋንቋነት መሰጠቱ የሚያበቃበትን የክፍል ደረጃ ክልሎች ይወስናሉ ብሏል፡፡…
Read More
በአማራ ክልል ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አልተመለሱም ተባለ

በአማራ ክልል ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አልተመለሱም ተባለ

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ እንዳስታወቀው በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ አቅዶ ነበር፡፡ ይሁንና ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ተማሪዎች 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ " ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 292 ሺሕ በላይ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 1.2 ሚሊዮን በላይ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 180 ሺሕ ተማሪዎች ተመዝግበዋል " ብሏል፡፡ " በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምዝገባው እየተካሄደ ነው፡፡ ትንሽ እሱ ላይ መዘግየት ይታያል፡፡ እስካሁን በጠቅላላ ወደ 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ናቸው የተመዘገቡት የእቅዱን ወደ 24 ፐርሰንት…
Read More
ዘጠኝ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ህጻናት ከትምህርት ገባታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ

ዘጠኝ ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ህጻናት ከትምህርት ገባታ ውጭ መሆናቸው ተገለጸ

የተባበሩት መንግስታት የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) ባወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 85 ሚሊየን ህጻናት በትምህርት ገበታ ላይ አይገኙም ብሏል። የሀገሪቱ የትምህርት ሁኔታ አሁንም በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ይገኛል ያለው ዩኒሴፍ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በሀገሪቱ በበርካታ ቦታዎች እየተባባሰ የመጣው ግጭት ነው ሲል ጠቁሟል። በተያዘው የፈረንጆቹ አመት የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት (ጥር፣ የካቲትና መጋቢት) በሀገሪቱ የተዘጉ ትምህርት ቤቶች ቁጥር በ18 በመቶ ጨምሯል ያለው ዩኒሴፍ ጉዳት የደረሰባቸው የትምህርት ቤቶችን ቁጥር በ5 ነጥብ 5 በመቶ መጨመሩንም ጠቁሟል። በሀገሪቱ 6 ሺ 770 ትምህርት ቤቶች ጉዳት ሲደርስባቸው 6 ሺ 410 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ተዘግተዋል ሲል በየሶስት ወሩ በትምህር ዙሪያ በሚያሳትመው ኒውስሌተር ላይ ባሰፈረው ሪፖርት አስታውቋል። በትምህርት ገበታ ላይ…
Read More
በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ 9 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በፀጥታ ችግር ምክንያት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 8.8 ሚሊዮን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። በኢትዮጵያ በግጭት ምክንያት 8,977 ትምህርት ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 6,483 ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆናቸውን በሚኒስቴሩ 'ትምህርትን በአደጋ ማስቀጠል' ባለሙያ ንጋቱ አበበ ተናግረዋል፡፡ ሚኒስቴሩ እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በመሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል ጥረት ቢያደርጉም፤ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች በቀጠሉት ግጭቶች ምክንያት ችግሩን ለመፍታት አስቸጋሪ እንደሆነ ባለሙያው ጠቁመዋል፡፡ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የመማር ማስተማር ሒደቱን ለማስቀጠል የሚጠበቅባቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉም ባለሙያው ጥሪ አቅርበዋል። ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ጦርነት እየተካሄደ ባለበት የአማራ ክልል ውስጥ 2 ነጥብ 6 ሚሊዮን…
Read More
ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን እንደሚመድብ ገልጿል፡፡ ይሁንና ስድስት የመንግስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ አስታውቋል፡፡ የሬሚዲያል ተማሪዎችን ከማይቀበሉ ዩንቨርሲቲዎች መካከልም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እነዚህ ዩንቨርሲቲዎች ለምን የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ምክንያታቸውን አልጠቀሰም፡፡ በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸው ይታወሳል፡፡ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ…
Read More
ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 817 ሺህ ተማሪዎች መውደቃቸው ተገለጸ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውስጥ 817 ሺህ ተማሪዎች መውደቃቸው ተገለጸ

1ሺህ 328 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ እንዳላሳለፉ ተገልጿል።በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የ2015  የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ 27 ሺሕ 267 ተማሪዎች ወይንም (ሦስት ነጥብ ኹለት በመቶ ብቻ) 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ውጤት አምጥተዋል። በተፈጥሮ ሳይንስ ከተፈተኑ 356 ሺሕ 878 ተማሪዎች ውስጥ 19 ሺሕ 017 ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ውጤት ሲመጡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ ከተፈተኑ 488 ሺሕ 221 ተማሪዎች ውስጥ 7…
Read More
በአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች በቡድን መደባደባቸው ተገለጸ

በአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች በቡድን መደባደባቸው ተገለጸ

በአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች በቡድን መደባደባቸው ተገለጸ በጎንደር ዩኒቨርስቲ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ፈታኝ እና ሁለት ፖሊሶች መገደላቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለመፈተን ከአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የመንግስት እና የግል ትምህርት ቤቶች ወደ ዩንቨርሲቲ የመጡ ተማሪዎች በቡድን መደባደባቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ላይ እንዳሉት በትምህር ቤቶቻቸው በመቧደን ተደባድበዋል ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የዶርም በር፣ ሎከር እና ሌሎች አካላዊ ጉዳት ደርሷል ብለዋል፡፡ ፖሊስ ክስተቱን እያጣራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ 87 ተማሪዎች ተይዘው ምርመራ በመካሄድ ላይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም ከአዲስ አበባ ውጪ በጎንደር እና በጋምቤላ የ12ኛ ክፍል ፈተና በተወሰነ ደረጃ መስተጓጎሉ ተገልጿል፡፡ በጎንደር በተከሰተው ግጭት ምክንያት 16 ሺህ…
Read More
ትምህርት ሚኒስቴር የሬሚዲያል ፈተናዎችን ሰረዘ

ትምህርት ሚኒስቴር የሬሚዲያል ፈተናዎችን ሰረዘ

የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን ወስደው ወደ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን የሬሚዲያል ፕሮግራም በመስጠት ለይ መሆኑ ይታወሳል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከትናንት ሰኔ 26 ቀን ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ፈተናን በያሉበት ሆነው በመፈተን ላይ ናቸው፡፡ ይሁንና ሚኒስቴሩ ይህ ፈተና መሰረዙን ያስታወቀ ሲሆን ምክንያቹን ከመናገር ተቆጥቧል፡፡ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ እንዲሁም ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ፕሮግራም ማሻሻያ እንደተደረገበትም ገልጿል፡፡ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ካምፓስ ያላቸውን…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም በያዝነው ዓመት ሕዳር ወር የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡ ይሁንና የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ የሕፃናት አድን ድርጅት/ሴቭ ዘ ችልድረን አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ እንዳለው የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ብሏል፡፡  በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሕፃናት በላይ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሰ 16 ኢትዮጵያውያን ሕፃናት መሃከል አንዱ ከትምህርት ገበታ መገለሉን ያሳያል ተብሏል፡፡ ይህ አሃዝ ኢትዮጵያን ከትምህርት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ቀውስ ካስተናገዱ ሃገራት አንዷ እንደሚያደርጋት ተገልጿል፡፡  በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሚገኙ…
Read More