EthioNegari

አሲያ ኽሊፋ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

አሲያ ኽሊፋ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 ሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመርጣለች፡፡ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓመታዊ የስልጠና መርሃ ግብር፣ ከሁዋዌ ታዋቂ የማኅበራዊ ኃላፊነት ስራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም ባለፈው ሳምንት የ2025 የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደሮችን መርጦ አሳውቋል። ከተመረጡት 12 አምባሳደሮች መካከል በኢትዮጵያ የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የአራተኛ ዓመት የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ የሆነችው አሲያ ኽሊፋ ትገኛለች። ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓላማውን ያደረገው በዓለም ዙሪያ ያሉ ወጣት ተማሪዎችን በአጭር ጊዜ ስልጠና  የዲጂታል ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አረዳዳቸውን ማሳደግ ነው። ለዚህም አጫጭር ስልጠናዎችን፣ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እና የተመራቂዎች ማህበር እንቅስቃሴዎች (አልሙናይ) ተሳትፎ እንዲጎለብት ይሰራል። የባህል ልውውጦች አስፈላጊነት እና የስራ ፈጣሪነት…
Read More
አዲስ አበባ የጦር መሳሪያ በታጠቁ ድሮኖች ትጠበቃለች ተባለ

አዲስ አበባ የጦር መሳሪያ በታጠቁ ድሮኖች ትጠበቃለች ተባለ

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲ አበባ የታጠቁ ድሮኖችን ለጸጥታ ስራ እንደሚጠቀም አስታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ አስተዳደር የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና ትራፊክ ፍሰት ለመቆጣጠር ይሰማራሉ የተባሉ ድሮኖች ቁጥጥር ብቻ ሳይሆን እርምጃም እንደሚወስዱ አስታውቋል። የትራፊክ ፍሰት እና በበዓላት ወቅት የከተማዋን ጸጥታ ለመቆጣጠር በርካታ ድሮኖች መግባታቸው እና የሚቆጣጠሯቸው ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ስልጠና አጠናቅቀው በቀጣይ ጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ስራ እንደሚገቡ ተገልጿል፡፡ ድሮኖቹ የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና የትራፊክ ፍሰት ከመቆጣጠር ባሻገር እርምጃም እንደሚወስዱ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ተናግሯል፡፡ በቅርብ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም ታላላቅ ፕሮግራሞችን ቁጥጥር ማድረግ የሚችሉ የድሮኖች ስምሪት እንደሚደረግ፣ የፀጥታ ጥምር ግብረ ኃይል ከቀናት በፊት መግለጹ ይታወቃል፡፡ አሁን ላይ በርካታ ድሮኖች…
Read More
መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

መንግሥት የጎዳና ተዳዳሪዎችን በግዴታ ወደ ማጎሪያ ስፍራ እያስገባ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በጎዳና ላይ ያሉ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው መያዝና ወደ ማቆያ ማዕከላት ማስገባት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን ስለሚያስከትል ሊቆም ይገባል ሲል  አሳስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት፣ ዓለም አቀፋዊና አህጉራዊ ጉባኤዎች እንዲሁም ከሌሎች ተመሳሳይ ኹነቶች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በኃይል በማንሳት በአንድ ስፍራ እንዲቆዩ የማድረግ ስራ በተደጋጋሚ እንደሚከናወን መግለጫው አመላክቷል፡፡ ኢሰመኮ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም ባደረጋቸው ክትትሎች በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ “ቃሊቲ አካባቢ” ተብሎ በሚጠራው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ አካባቢ ሰፊ መጋዘን ውስጥ ከጎዳና ላይ የተነሱ በርካታ ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ወደ ማቆያው ከገቡት ሰዎች መካከል በማዕከሉ ከመቆየት እና የእርሻ ሥራ ከመሥራት እንዲመርጡ በማድረግ፤ የእርሻ…
Read More
ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ጸደቀ መመሪያው በመንገዶች ግራና ቀኝ በየ50 ኪሎሜትር ልዩነት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሙላት የሚችል ፈጣን ቻርጀር ጣቢያ ማቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ይሁንና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል ማቅረብ የሚፈልጉ ተቋማት ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድ በመውሰድ እንዳለባቸው መመሪያ ይገልጻል። በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ሃይል መሙያዎች ከባለስልጣኑ ፈቃድ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በግል በቤት ውስጥ ከሚተከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል መሙሊያ ማሽኖች ፈቃድ መጠየቅ የማይጠበቅባቸው መሆኑን ያመላከተው የተቋሙ መረጃ ከዚህ ውጭ ግን ማናቸውም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል ሙሌት የሚሰጡ ማሽኖች መትከል የሚቻለው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑንም አመላክቷል። መመሪያው ለህዝብ በሽያጭ የኤሌክትሪክ ሃይል ሙሊት አገልግሎት የሚሰጡ ታሪፋቸው በባለስልጣኑ ሲጸድቅላቸው…
Read More
ሲዳማ ክልል እንዲሆን ብዙ ዋጋ ብንከፍልም የጠበቅነውን ለውጥ ማየት አልቻልንም ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ

ሲዳማ ክልል እንዲሆን ብዙ ዋጋ ብንከፍልም የጠበቅነውን ለውጥ ማየት አልቻልንም ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ

የክልሉ መንግስት ግን በዓመት ከ60 ሺህ በላይ የስራ እድል እየፈጠርኩ ነው ሲል የፖለቲካ ፓርቲዎች ደግሞ የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ ክልል እንሁን ከሚል ወደ ልማት ጥያቄ ዞሯል ብለዋል በቀድሞው የደቡብ ክልል ስር ከነበሩ ዞኖች መካከል አንዱ የነበረው የሲዳማ ዞን ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ 11ኛው የኢትዮጵያ ክልል ሆኖ ተዋቅሯል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት በአራት ዞኖች እና አንድ ከተማ አስተዳድር የተዋቀረው ሲዳማ ክልል ከህዝበ ውሳኔ በኋላ ህይወት እንዴት እየቀጠለ እንደሆነ ኢትዮ ነጋሪ የክልሉን ነዋሪዎች አነጋግራለች፡፡ ለደህንነቱ በመስጋት ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ እንዳለን ከሆነ “ሲዳማ ክልል እንዲሆን ቤተሰቤን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ዋጋ ከፍለናል፡፡ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው እየተጠቀሙ ያሉት፣ ስራ ማግኘት አልቻልንም” ሲል ተናግሯል፡፡ “ሲዳማ…
Read More
ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ የስቶክ ማርኬት ገበያን ከ50 ዓመት በኋላ ዳግም አስጀመረች

ኢትዮጵያ በአጼ ሀይለስላሴ አስተዳድር ዘመን የስቶክ ግብይት የሚፈቅድ ስርዓት የነበራት ቢሆንም በደርግ ዘመን ተቋርጦ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ከ50 ዓመት በኋላ የስቶክ ግብይትን ዳግም ያስጀመረች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡ በዚህ የግብይት ስርዓት መሰረት ኩባንያዎች አክስዮኖቻቸውን በይፋ ለገዢዎች መሸጥ የጀመሩ ሲሆን ሸማቾች ደግሞ ለሚገዙት አክስዮን ዋስትና የሚሰጥ ተቋምም ወደ ስራ ገብቷል፡፡ ይህን የአክስዮን ግብይት የሚያሳልጡ ሁለት መንግስታዊ ተቋማት የተቋቋሙ ሲሆን የኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት እና የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋዮች ገበያ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የስቶክ ግብይትን ከአንድ ዓመት በፊት የመጀመር እቅድ የነበራት ቢሆንም ዘግይቶ ተጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ስር 39 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው የመንግስት…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ባሉ ዲፕሎማቶች ላይ የጉዞ ገደብ ጣለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ባሉ ዲፕሎማቶች ላይ የጉዞ ገደብ ጣለች

መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ደብዳቤ ተላከላቸው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መቀመጫውቸን በአዲስ አበባ ላደረጉ ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ሳያሳውቁ ከከተማ እንዳይወጡ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ከአንድ ሳምንት በፊት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተላከው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በአገሪቱ ድንበር ውስጥ ለሚያደርጓቸው ማናቸው እንቅስቃሴዎች ቅድመ ፈቃድ እንዲጠይቁ አሳስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ለሚገኙ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ተቋማት፣ ዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ድርጅቶችና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት፣ ከአዲስ አበባ ውጭ የሚያደርጓቸውን ጉዞዎች በተመለከተ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተቀመጠ የቅድሚያ ማሳወቂያ ፎርም ከሞሉ በኋላ መሆን እንዳለበት አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ ለዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተጻፈው ደብዳቤ ማስጠንቀቂያው ለሥራ ወይም ለግል ጉዳይ የሚጓዙትን እንደሆነ በግልጽ አያስረዳም ሲል…
Read More
የቻይና ኩባንያዎች ከ300 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል ፈጥረዋል ተባለ

የቻይና ኩባንያዎች ከ300 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል ፈጥረዋል ተባለ

ኢትዮጵያ በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ከሳበችው ውስጥ ግማሹ በቻይናዊን የተያዘ እንደሆነ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከቻይና ንግድ ምክር ቤት እና ከቻይና ኢምባሲ ጋር በአዲ አበባ ተወያይተዋል፡፡ ኮሚሽኑ በዚህ ጊዜ እንደገለጸው ባለፉት አምስት አመታት በኢትዮጵያ ከተጀመሩ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 50 በመቶ የሚሆኑት በቻይና ባለሀብቶች የለሙ ናቸው፡፡ ውይይቱ የቻይና ባለሀብቶችን ለማበረታታት የተዘጋጀ ሲሆን ውይይቱ ለቻይና ባለሀብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢን ለመፍጠር እና ተጨማሪ ባለሀበቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል፡፡ አሁን ላይ ቻይና በኢትዮጵያ ከ 3 ሺህ 300 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀከቶችን በማልማት ላይ ናት የተባለ ሲሆን ቻይና በኢትዮጵያ ከ325 ሺህ በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን የስራ እድሎች ፈጥራለችም ተብሏል፡፡ ከሶስት ወራት በፊት…
Read More
ሐዋሳን ጨምሮ በሲዳማ ክልል ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ምን ላይ ናቸው?

ሐዋሳን ጨምሮ በሲዳማ ክልል ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ምን ላይ ናቸው?

ጾታዊ ጥቃት በሰዎች ላይ አካላዊ፣ ወሲባዊ ወይም ስነ ልቦናዊ ችግሮችን የሚያስከትልና ጾታን መሰረት አድርጎ የሚፈፀም የኃይል ድርጊት ነው፡፡ ፍቅርተ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ስትሆን በምትኖርበት ከተማ ውስጥ የጾታዊ ጥቃት ምን እንደሚመስል ለጠየቅናት ጥያቄ ተከታዩን ምላሽ ሰጥታናለች፡፡ “ጾታዊ ጥቃት በቅርብ ሰው፣ በምናውቀው ሰው ነው የሚፈጸመው፡፡ በከተማዋ እና አቅራቢያ ብዙ አይነት ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እንዳሉ ይሰማኛል” ብላለች፡፡ “ወደ አደባባይ ያልወጡ ብዙ የጾታ ጥቃት ወንጀሎች አሉ” የምትለው ፍቅርተ “በቅርቡ የ14 ዓመት ጓደኛዬ በአጎቷ ተደፍራለች፡፡ እናት እና አባቷ ለማህበራዊ ጉዳይ ከቤታቸው ሲሄዱ አጎቷ ጋር እንድትሆን ብለው በአደራ አስቀመጧት፡፡ ነገር ግን የተሻለ ደህንነት አለው ብለው ባስቀመጧት ቤት ያስቀመጧት ይህች የ14 ዓመት ታዳጊ አጎቷ አስገድዶ ደፍሯታል፡፡…
Read More
በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ባጋጠመው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ 80 ሺህ ዜጎች እንደሚፈናቀሉ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች እየተደጋገሙ ሲሆን እስካሁን መኖሪያ ቤቶች ላይ የተወሰኑ ጉዳቶችን ከማድረስ የዘለለ ከባድ ጉዳት አላደረሱም፡፡ ባለፉት ሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 ጊዜ በላይ በአፋር ክልል አዋሽ ከተማ አቅራቢያ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ከ60 ዓመት በኋላ ከፍተኛ የጠባለ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት እንደገለጸው ከሆነ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አጋጥሟል፡፡ በዚህ አደጋ ምክንያት በአፋር ክልል ባሉ መኖሪያ ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት ላይ አነስተኛ ጉዳት ያጋጠመ ሲሆን ንዝረቱ አዲ አበባ ድረስ ተሰምቷል፡፡ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው ማስታወቂያ የርዕደ መሬቱ ማዕከል ከሆኑ 12 ቀበሌዎች 80 ሺህ ዜጎችን ሊፈጠር…
Read More