በጋሞ ዞን ባጋጠመ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱ ተገለጸ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ፣ካምባ እና ቦንኬ በተባሉ ወረዳዎች በደረሰው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 107 መድረሱን የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
ከሟቾቹ መካከል ከጋጮ ባባ ወረዳ ብቻ 102፣ ከካምባ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቦንኬ ወረዳ 3 በድምሩ የ107 ሰዎች ሕይወት ማለፉን አስተዳዳሪው ገልጸዋል።
አስተዳዳሪው አክለውም እስካሁን በተከናወነው አስቸጋሪ ፍለጋ የ57 ሰዎች አስክሬን መገኘቱ...