ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢ ቡድንን እንዲመሩ ተመረጡ
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ 73 አባላትን ያቀፈ የአፍሪካ ኅብረት ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው የኢትዮጵያ ምርጫ 2018 ታዛቢ ልዑካን ቡድን ይመራሉ ተብሏል።
በቀድሞው የኬኒያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው፣ የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባቱን ኅብረቱ አስታውቋል።
ታዛቢ ቡድኑ ከ37 አገራት የተውጣጡ 73 አባላትን ያቀፈ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ከታዛቢዎቹ ውስጥ 61 በመቶዎቹ ሴቶች እንደሆኑ ተገልጿል።
...