ከ46 ሚሊዮን ብር በላይ በማጭበርበር ወንጀል ሲፈለግ የነበረው ኢትዮጵያዊ በኢንዶኔዥያ ተያዘ
ከ46.4 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸውን 12 ቢዋይዲ ሴጉል የኤሌክትሪክ ተሽከርካረዎችን በውክልና ለመሸጥ ከግል ተበዳይ ዮናስ ገብረመስቀል ከተረከበ በኋላ ገንዘቡን ሳያስረክብ ከባድ የማታለል ወንጀል ፈጽሞ ከሀገር የተሰወረው ሰልማን መሀመድ የተባለው ግለሰብ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና በኢንተርፖል ትብብር በኢንዶኔዥያ ሀገር በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገልጿል።
ተጠርጣሪው ከኢትዮጵያ ወጥቶ በታይላንድ፣ በሲንጋፖር፣ በፊሊፒንስና በኢንዶኔዥያ ሀገራት ከሕግ ተጠያቂነት ለማ...