ባህርዳር ስታዲየም የካፍ እውቅና ተሰጠው
ባሕርዳር ስታዲየም ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ተፈቅዶለታል።
የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስፈርቶችን በማሟላት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ፈቃድ አግኝቷል።
ኢትዮጵያ የካፍ እና ፊፋ እውቅና ያለው ስታዲየም ባለቤት ባለመሆኗ ዋልያዎቹን ጨምሮ ክለቦች በውሰት ሜዳዎች ሲጫወቱ ቆይተዋል።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም መስፈርቶችን ባለማሟላቱ ዓለምአቀፍ ጨዋ...