የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ባለበት እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደረሰ
ከአንድ ወር በላይ የቆየው የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች እየተወያዩባቸው ካሉ ጉዳዮች መካከል የሰንደቅ አላማ ጉዳይ አንዱ ሲሆን አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለም ባለበት እንዲቀጥል ነገር ግን መሀሉ ላይ ያለው አርማ እንዲቀየር ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
ከ8ቱም ቡድኖች በተመረጡ አጠናቃሪዎች የተዋቀረው አዘጋጅ ቡድን እያንዳንዳቸው 500 ሰዎችን ከያዙ 8 ቡድኖች ተቀብሎ ያጣጣማቸውን፣ ድግግሞሽ እንዳይኖር ያስወገደላቸውን የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች አዘጋጅቶ የ8ቱንም ቡድኖች...