19
Jun
ከተመደበው በጀት ውስጥ ትልቁን ድርሻ የያዘው ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ በሚል የተመደበው ነው ተብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ሰኔ 12፣ 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የከተማዋን የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሰረት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚጀምረው የ2019 በጀት ዓመት የአዲስ አበባ ከተማ በጀት 502 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ሆኖ ወደ ምክር ቤት እንዲመራ መመርያ ሰጥቷል ። ረቂቅ በጀቱ የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣ድህነትን ለመቀነስ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማረጋገጥ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ ተዘርዝሯል። በተጨማሪም የከተማውን ነዋሪ የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት አቅርቦት ለማሳደግ በተለይም የስራ እድል ፈጠራን ለሚያበረታቱ የመሰረተ…