Business

ለአዲሰ አበባ ከተማ ዓመታዊ በጀት 502 ቢሊዮን ብር ተመደበ

ለአዲሰ አበባ ከተማ ዓመታዊ በጀት 502 ቢሊዮን ብር ተመደበ

ከተመደበው በጀት ውስጥ ትልቁን ድርሻ የያዘው ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ በሚል የተመደበው ነው ተብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ሰኔ 12፣ 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የከተማዋን የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሰረት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚጀምረው የ2019 በጀት ዓመት የአዲስ አበባ ከተማ በጀት 502 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ሆኖ ወደ ምክር ቤት እንዲመራ መመርያ ሰጥቷል ። ረቂቅ በጀቱ የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣ድህነትን ለመቀነስ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማረጋገጥ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ ተዘርዝሯል። በተጨማሪም የከተማውን ነዋሪ የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት አቅርቦት ለማሳደግ በተለይም  የስራ እድል ፈጠራን ለሚያበረታቱ የመሰረተ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ዓለም ባንክ ከአንድ ወር በኋላ ለኢትዮጵያ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በጀት ድጋፍ ሊያጸድቅ መሆኑን ገልጿል። አንድ የባንኩ ከፍተኛ ባለሙያ ሲናገሩ አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የገንዘብ ሚኒስቴር ከሳምንት በፊት የ2019 ዓ.ም የበጀት ረቂቀን ለምክር ቤቱ ባቀረበበት ወቅት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ መሆኑን ገልፆ የበጀት ጉድለቱ ከውጭ እርዳታ እና ሀገር ውስጥ በሚገኝባቸው ገቢ ይሸፈናል ማለቱ ይታወሳል። በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ የግሉ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ብስራት ተሾመ እንደገለጹት ከሆነ ባንኩ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚውል የአንድ ጊዜ የበጀት ድጋፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ባለሙያው ይህን ያሉት ትናንት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር ባዘጋጁት የውይይት መድረክ…
Read More
ጁንቱ ቴክኖሎጂ የ“ቼሪ” ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ ጀመረ

ጁንቱ ቴክኖሎጂ የ“ቼሪ” ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ ጀመረ

“ጁንቱ ቴክኖሎጂስ ግሩፕ” የ“ቼሪ” አውቶሞቢል ኩባንያ (Chery Automobile) ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ መጀመሩን አስታወቀ፡፡  ድርጅቱ “ኦሞዳ” (OMODA E5) እና “ጃይኮ” (JAECOO J5) የተሰኙትንና የ“ቼሪ” ምርቶች የሆኑትን ሁለት የኤሌክትሪክ መኪና ሞዴሎችን ለኢትዮጵያ ገበያ በማቅረብ የዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ወኪል አቅራቢነቱን ማስፋፋቱን ገልጿል፡፡   ድርጅቱ ስራውን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታወቀ አገልግሎት፣ በላቀ ቴክኖሎጂ እና በረጅም ጊዜ የገበያ ኢንቨስትመንት ለመምራትም “የጁንቱ-ኦሞዳ-ጃይኮ” የምርት ማሳያ (ሾውሩም) እና የድህረ ሽያጭ አገልግሎት ማዕከሉን ሰሞኑን ስራ አስጀምሯል።  የጁንቱ ቴክኖሎጂስ ትሬዲንግ የኦሞዳ እና ጃይኮ ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክንዴ መቻል፣ ጁንቱ ቴክኖሎጂስ ከሁለት ወራት በፊት አራት ዓይነት የ“ጂ.ኤ.ሲ” (GAC) የኤሌክትሪክ መኪና ሞዴሎችን ለገበያ ማቅረቡን አስታውሰው፣ በቅርቡ ደግሞ “ኦሞዳ” እና “ጃይኮ” የተሰኙትና…
Read More
መንግስት በቀጣዩ ዓመት 1 ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

መንግስት በቀጣዩ ዓመት 1 ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

የፌደራል መንግሥት በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡ ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት ያለው ሆኗል። እቅዱ ከዓመታዊ በጀት  ውስጥ የ89  በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ሚንስትሩ አቶ አህመድ ጠቁመዋል። የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ…
Read More
ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡ ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡ በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት…
Read More
ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ

ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል። ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል። ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው። በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው…
Read More
ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

ብሔራዊ ባንክ አስመጪዎች እና ላኪዎች ያለ ባንክ ቅድመ እውቅና እቃ እንዲያዙ ፈቀደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት እያደረገ ያለውን ሽግግር ለማጠናከር፣ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን የሚያቀሉ አዳዲስ መመሪያዎችን ይፋ አድርጓል።ባንኩ ባወጣው መግለጫ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን ይበልጥ ለማቅለልና በንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት የሆኑ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶችን የሚያሳጥሩ ናቸው።በአዲሱ መመሪያ መሰረት የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ እና የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ሂሳብ  ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ እና የሰነድ መክፈያ ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል።ይህ ማሻሻያ በተለይ በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ነጋዴዎች የጊዜና የቢሮክራሲ ጫናን ያቀላል ተብሎ ይጠበቃል።በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ያላቸው ተቋማት የባንኮችን ቅድመ ፈቃድ ሳይጠብቁ በሰነድ መክፈያ ስምምነት መሠረት የሸቀጦችን የጭነት ትዕዛዝ መስጠት…
Read More
ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች የ100 ሺህ ብር ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተባለ

በግብይት ወቅት ማናቸውም ግብር ከፋይ ነጋዴ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲያከናውን ወይም ዋጋ አሳንሶ የተገኘ በእያንዳንዱ ደረሰኝ የአንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት መጣል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። ያለ ደረሰኝ ሲገበያይ የተገኘ ማንኛውም ግብር ከፋይ ለገዢ ባልሰጠው በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብዛት ከዚህ ቀደም 50 ሺህ ብር ይቀጣ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ማሻሻያ በተደረገለት የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ መሰረት ወደ አንድ መቶ ሺህ ብር ቅጣት ከፍ ብሏል።የገንዘብ ሚኒስቴር እንደ ዋና ማሻሻያዎች ካነሳቸው መካከል የታክስ የምስክር ወረቀት አሰጣጥን ማሻሻል፣ የታክስ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በማስታረቅ ሥርዓት መፍታት፣ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የሚታረምበትን ሥርዓት ግልጽ ማድረግ፣ እንዲሁም የውሳኔ ማስታወቂያ ማሻሻያና የይግባኝ ማቅረቢያ የጊዜ ገደቦችን በግልጽ ማስቀመጥ የሚሉት ይገኙበታል።እነዚህ…
Read More
ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

ባለፉት 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 8.7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

በተያዘው የ2018 በጀት ዓመት በ10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ  8.71 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር አስታውቋል። በ2018 በጀት ዓመት የ10 ወራት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ከታቀደው ግብ በላይ ውጤት መመዝገቡን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 10 ወራት ውስጥ ከወጪ ንግድ 7.25 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ፣ 8.71 ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን አስታውቀዋል። የወጪ ንግድ አፈጻጸም ባለፈው ዓመት (2017 ዓ.ም) ተመሳሳይ ወቅት ከተመዘገበው የ6.08 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ43.32 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ሚንስትሩ አብራርተዋል። ይህ ስኬት በዋናነት በንግድ ዘርፉ ላይ የተወሰዱ የፖሊሲ እርምጃዎች ውጤት መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመው፤ በላኪዎችና በዘርፉ ተዋንያን መካከል የተፈጠረው…
Read More
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

ተቋሙ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽመዋል ያላቸውን 1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ እርምጃመውሰዱን አስታውቋል።  እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ሲሆን ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስጃለሁ ብሏል፡፡   በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103…
Read More