Business

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሙስና ምክንያት 16 ሰራተኞችን ከስራ አሰናበተ

ተቋሙ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽመዋል ያላቸውን 1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ እርምጃመውሰዱን አስታውቋል።  እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ሲሆን ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስጃለሁ ብሏል፡፡   በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ወራት ውስጥ ከኪሳራ ወደ ትርፍ እንደሚሸጋገር አስታወቀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ወራት ውስጥ ከኪሳራ ወደ ትርፍ እንደሚሸጋገር አስታወቀ

ከአምስት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ማድረጉን ገልጿል። ለኢንቨስትመንት ያወጣውን ወጪ ሳይመልስ የቆየው ኩባንያው ኪሳራው እየቀነሰ መምጣቱን ገልጾ በቀጣዮቹ ወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፍ እንደሚገባ አስታውቋል። መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ130 በመቶ ብለጫ አንዳለው የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄሌፑት ገልጸዋል፡፡ በጊዜው ኩባንያው 39.5 ቢሊዮን የኬንያ ሽልንግ ወይም 47.7 ቢሊዮን ብር አካከባቢ ኪሳራ አስመዝግቧል፡፡ ኪሳራው አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከተመዘገበው በግማሽ ያህል መቀነሱንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል፡፡ ኩባንያው በዓመቱ ውስጥ ካገኘው 15.9 ቢሊዮን ብር ውስጥ 9.6…
Read More
ምርጫ ቦርድ 22 ምርጫ ጣቢያዎች መዘጋታቸውን ገለጸ

ምርጫ ቦርድ 22 ምርጫ ጣቢያዎች መዘጋታቸውን ገለጸ

በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮችን ምዝገባ እንዲያከናውኑ ከተከፈቱ ምርጫ ጣቢያዎች መካከል 22ቱ ህገወጥ ድርጊት በመፈጸማቸው ምክንያት መዘጋታቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። ለ45 ቀናት ሲካሄድ የነበረው የመራጮች ምዝገባ መጠናቀቁን አስመልክቶ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ሀይሉ በሰጡት መግለጫ የመራጮች ምዝገባ 50 ሚሊዮን ማለፉን ተናግረዋል፡፡ የተዘጉት የምርጫ ጣቢያዎች ተመሳሳይ መራጭ በተለያዩ የምርጫ ጣቢያ ላይ ተመሳሳይ ፊርማ የተገኙባቸውም አሉ ብሏል።  ቦርዱ መስራት የሚጠበቅባቸውን ስራ ወደ ጎን በመተው ህግን ያላከበረ አሰራር መከተላቸውንም አመልክቷል። በተመሳሳይ እንዲህ ዓይነት ድርጊት ላይ የተሳተፉ የምርጫ አስፈፃሚዎችም ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ቦርዱ እርምጃ እንደወሰደ ቢገልጽም በምን ያህሎቹ ላይ እንደወሰደ ግን ያለው ነገር የለም።  ቦርዱ ከዚህ ቀደም በደመወዝ እና በተለያዩ ጉዳዮች…
Read More
ከ300 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መሰማራታቸው ተገለጸ

ከ300 በላይ የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መሰማራታቸው ተገለጸ

የኢትዮጵያ- የአውሮፓ ህብረት የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ሲሆን ነገ ፍጻሜውን ያገኛል ተብሏል። የኢትዮጵያን እና አውሮፓን ንግድ እና ኢንቨስትመንት ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ ጉባኤ መሪዎች፣ የንግድ አማካሪዎች፣ የኩባንያ ባለቤቶች እና ሌሎችም ተገኝተውበታል፡፡ በጉባኤው ላይ የተገኙት የአውሮፓ ህብረት የአለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽር ጆሴፍ ሲኬላ እንዳሉት 300 የሚጠጉ የአውሮፓ ሀገራት ኩባንያዎች በተለያዩ ዘርፎች በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ በኢንቨስትመንት ላይ ናቸው ብለዋል። በሌላ በኩል የአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ የንግድ ቀጠናን ተግባራዊት ለማፍጠን የሚያግዝ 1.2 ቢሊዮን ዮሮ ድጋፍ ስምምነትም በፎረሙ ላይ ተፈርሟል። ከዚህ በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት አቋርጦት የነበረውን የበጀት ድጋፍ ዳግም መጀመሩ ተገልጿል። በዚህም ህበረቱ ለኢትዮጵያ መንግስት የበጀት ድጋፍ 140 ሚሊዮን…
Read More
በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ያሉ ነጋዴዎች ከግብር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ተወሰነ

በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ያሉ ነጋዴዎች ከግብር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ተወሰነ

በነጻ የንግድ ቀጠናዎች ውስጥ ግብአቶችን እና ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከገቢ ግብር ነጻ እንዲሆኑ ተወሰነ:: የገንዘብ ሚኒስቴር ለገቢዎች ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት በሚፈለገው መጠን እንዳያድግ ምክንያት ከሆኑት መካከል የካፒታል እጥረት፤ የግብአት አቅርቦት ችግር  እና የባለሙያ እጥረት በዋንኛነት ምክንያት አስቀምጧል፡፡ እነዚህን ችግሮች ደረጃ በደረጃ በማቃለል የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪ ልማትን  ማሳደግ አእንደሚገባ በደብዳቤው ላይ ጠቅሷል፡፡ ግብአቶች እና ሌሎችም ምርቶች በበቂ መጠን ለገበያ እንዲቀርቡ ለማድረግ አስመጪዎች ምርቱን ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት የሚከፍሉት ቀረጥ እና ታክስ ውስን የሆነውን ካፒታላቸውን በመያዝ ረገድ የሚያሳድረባቸውን ጫና ማቃለል እንደሚያስፈልግ አስታውቋል። አስመጪዎች  ግብቶችን  እና ምርቶችን ቀረጥ እና ታክስ ሳይከፍሉ ወደ አገር ውስጥ አስገብተው ለግብአቱ…
Read More
የቻይናው ጓንዡ አውቶሞቢል ግሩፕ በኢትዮጵያ መኪና ማምረት እንዲጀምር ተጠየቀ

የቻይናው ጓንዡ አውቶሞቢል ግሩፕ በኢትዮጵያ መኪና ማምረት እንዲጀምር ተጠየቀ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ኩባንያው ከሽያጭ ማዕከል መክፈት በተጨማሪ የማምረቻ እና መገጣጠሚያ ማዕከልም እንዲከፍት ጠይቀዋል። GAC JUNTU አዲስ ዘመናዊና ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሠራ የትራንስፖርት ሥርዓት በማስተዋወቅ፣ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ቀዳሚ የኤግዚቢሽን ማዕከሉን በአዲስ አበባ በይፋ መርቋል። የኩባንያው  የምርት ማሳየ 2,300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው  ሲሆን ከማሳያነት ባለፈ  ከሽያጭ በኋላ  አገልግሎት፣  መለዋወጫ እና በአምራች የተደገፈ ዋስትና የሚሰጥበት አካቷል ተብሏል። ተቋሙ የተሽከርካሪ ሽያጭን፣ የተረጋገጠ የድኅረ-ሽያጭ አገልግሎትን፣ ኦሪጅናል የመለዋወጫ ዕቃዎችን እና ከአምራቹ የሚሰጥ ዋስትናን ያካተተ የተሟላ የ4S-ደረጃ ሥርዓት (4S-standard ecosystem) በማቅረብ በኢትዮጵያ ለታማኝነትና ለደንበኞች አገልግሎት አዲስ መለኪያ ያስቀምጣል። GAC JUNTU የኢትዮጵያን ገበያ  አራት ዘመናዊ  የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ይዞ መቅረቡን…
Read More
ጊፍት ሪልስቴት ከ1200 በላይ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ

ጊፍት ሪልስቴት ከ1200 በላይ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ

በኢትዮጵያ የቤት ልማት ፕሮግራም ወይም ሪልኢስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ አንዱ የሆነው ጊፍት ሪል ስቴት በ15 በመቶ ቅናሽ ለፋሲካ በዓል የአፓርትመንትና የንግድ ሱቆችን ለሽያጭ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ የድርጅቱ ሽያጭ እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር አቶ ብርቁ ይርጋ በአዲስ አበባ ለገሀር ሳይት በተዘጋጀ ፕሮግራም ላይ እንዳሉት ጊፍት ሪል ኢስቴት ደንበኞች የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በ2 በመቶ ቅድመ ክፍያ ብቻ ቤት መግዛት እንዲችሉ የሚያስችል ኤክስፖ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል። የሽያጭ ኤክስፖው ከመጋቢት 19 እስከ ሚያዚያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን 1 ሺህ 200 ቤቶች ለሽያጭ መቅረባቸውን ዳይሬክተሩ ተገልጿል። በ2005. የተመሰረተው ጊፍት ሪል ስቴት ሦስት መንደሮችን ጨርሶ ለገዢዎች አስረክቧል የተባለ ሲሆን አራተኛውን የጊፍት ሜትሮፖሊታን መንደር በለገሃር ላይ 4 ሺህ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ የኢንሹራንስ ባለአክሲዮኖችን ለመመዘን አዲስ መመሪያ አወጣ

ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪያ በኢንሹራንስ ዘርፉ ላይ ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትን እና የተጠናከረ የኮርፖሬት አስተዳደርን ለማስፈን ያለመ ነው ብሏል። በዚህ መመሪያ መሠረትም ማንኛውም የኢንሹራንስ ኩባንያ የቦርድ አባላት ስብጥር አንድን ጾታ ብቻ የያዘ መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ቢያንስ ሁለት ሴት የቦርድ አባላት ሊኖሩት እንደሚገባ መመሪያው የግዴታ መስፈርትን አስቀምጧል። በተጨማሪም አንድ የቦርድ አባል ለመሆን ዝቅተኛው የዕድሜ ገደብ 30 ዓመት መሆን እንዳለበት ተደንግጓል። እያንዳንዱ የኢንሹራንስ ኩባንያ ሦስት ገለልተኛ የቦርድ አባላት ሊኖሩት ይገባል የተባለ ሲሆን እነዚህ ግለሰቦች የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው እና በፋይናንስ ዘርፍ ወይም ተያያዥ መስኮች የ10 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል ተብሏል። እንደ መመሪያው ከሆነ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች በገለልተኛ የቦርድ…
Read More
በተፈጥሮ ጋዝ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች አዲስ አስገዳጅ ደረጃዎች መውጣቱ ተገለጸ

በተፈጥሮ ጋዝ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች አዲስ አስገዳጅ ደረጃዎች መውጣቱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ መጠቀም መጀመሯን ተከትሎ አስገዳጅ ደረጃዎች ማዘጋጀቱን ገልጿል። የኢንስቲትዩቱ ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ በሰጡት መግለጫ 79 አጠቃላይ ደረጃዎችን መዘጋጀታቸውን ገልጸው ከዚህ ውስጥ ሰባቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ደረጃዎች እንደሆኑ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት በሀገር ውስጥ ለሚገጣጠሙ እና ከውጭ ለሚገቡ በነዳጅ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ደረጃዎች እንዳሏት የተናገሩት ዶክተር መሰረት በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ግን የሚመዘኑበት የጥራት ማስጠበቂያ ደረጃ እንዳልነበራት አክለዋል፡፡ አዲሱ ደረጃ የተፈጥሮ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ሲገጣጠሙ ሊሟሉ የሚገቡ መስፈርቶችን የያዘ እንደሆነም ተገልጿል። በኢንስቲትዩቱ የደረጃዎች ዝግጅት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ይልማ መንግስቱ በሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ጥራት ለማስጠበቅ የወጣው ደረጃ በሶማሊ ክልል የተገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ መጠቀም በመጀመሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ አዲሱ ደረጃ የተፈጥሮ ጋዝ የሚጠቀሙ ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ ምን ምን መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚገባቸው…
Read More
ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያ በአማራ ክልል ግብር የድጅታል ገንዘብ አገልግሎት ለመስጠት ተስማማ

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የታክስ ክፍያዎችን በኤም-ፔሳ የዲጂታል ስርዓት ለመሰብሰብ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ በሆነው ኤምፔሳ_ኢትዮጵያ እና የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ መካከል በባህር ዳር ከተማ ተፈርሟል። ግብር ከፋዮች ከዚህ በኋላ ኤም-ፔሳን በመጠቀም ግብራቸውን ካሉበት ሆነው በዲጂታል አማራጭ በቀላሉ መክፈል ይችላሉ ተብሏል። ከ477 ሺህ በላይ ግብር ከፋዮች ያሉት የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2017 የግብር ዘመን 67 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር) ተናግረዋል። በ2018 በጀት ዓመትም ክልሉ 100.37 ቢሊየን ብር የመሰብሰብ እቅድ ያለው ሲሆን ከዚህ ውስጥ እስካሁን 60 በመቶ የሚሆነውን ሰብስቧል ብለዋል። የታቀደውን ገቢ መሰብሰብ የሚቻለው በዲጂታል አማራጭ በመታገዝ ግብርን በቀላሉና…
Read More