Business

ከ18 ወራት በኋላ በሚካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ 40 አገራት ያህል አድማ ሊመቱ ይችላሉ ተባለ

ከ18 ወራት በኋላ በሚካሄደው የፓሪስ ኦሊምፒክ 40 አገራት ያህል አድማ ሊመቱ ይችላሉ ተባለ

ከዓመት ከስድስት ወር በኋላ የሚካሄደውን የፓሪስ ኦሊምፒክ እስከ 40 አገራት ያክል አድማ ሊመቱ እንደሚችሉ ፖላንድ አስጠነቀቀች። የፖላንድ የስፖርት እና ቱሪዝም ሚኒስትር ካሚል ቦርትኒዙክ የፓሪስ ኦሊምፒክ ትርጉም አልባ ሊሆን ይችላል ብለዋል። ይህ የሚስትሩ አስተያየት የተሰማው ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በፓሪሱ 2024 ኦሊምፒክ የሩሲያ እና ቤላሩስ ዜጋ አትሌቶች እንዲሳተፉ ለመፍቀድ ማቀዱን ፖላንድ፣ ሊቱኒያ፣ ኢስቶኒያ እና ላትቪያ በጋራ መቃወማቸውን ተከትሎ ነው። ዩክሬን የሁለቱ አገራት አትሌቶች የሚሳተፉ ከሆነ በውድድሩ አልገኝም ብላለች። የኦሊምፒክ ኮሚቴው ግን በውድድሩ ላይ አድማ ማድረግ ትርፉ “አትሌቶችን መቅጣት ብቻ ነው” ብሏል። የፖላንድ የስፖርት እና የቱሪዝም ሚንስትሩ የዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ከሳምንት በኋላ ከሚያደርገው ስብሰባ በፊት ግሬት ብሪቴን፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳን…
Read More
የኳታሩ ሼክ ጃሲም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት መዘጋጀታቸውን አስታወቁ

የኳታሩ ሼክ ጃሲም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት መዘጋጀታቸውን አስታወቁ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጉልህ ታሪክ ያለው እና በዘንድሮው የውድድር ዘመን ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ባለሃብቶች ጥያቄያ አቅርበዋል። ከኳታር ትልልቅ ባንኮች የአንደኛው ሊቀ መንበር የሆኑት ሼክ ጃስሚ ቢን ሃማድ አል ታኒ ፋውንዴሽናቸው ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ጥያቄ ማቅረቡን አረጋግጠዋል። ቢቢሲ መረዳት እንደቻለው የሰር ጂም ራትክሊፍ ንብረት የሆነው ኢኒዎስም ማንችስተር ዩናይትድን ለመግዛት ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል። ቢሊዮነሩ ራትክሊፍ ማንችስተር ዩናይትድን የመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ቀድመው አሳውቀው ነበር። በ2005 (እአአ) ማንችስተር ዩናይትድን የገዙት የግሌዘር ቤተሰቦች “ስትራቴጅክ አማራጮችን መፈለግ” በሚል ክለቡን ለመሸጥ አስበዋል። የኳታሩ ሼክ ጃሲም ክለቡን ወደ ቀድሞ ክብሩ የመመለስ ዕቅድ አለን በማለት ቡድኑን ቢገዙ ሊያደርጉ ያሰቡትን ገልጸዋል። የእግር ኳስ ቡድኑን ማጠናከር፣ የልምምድ…
Read More
በአፍሪካ የስፖርት ውድድሮች ላይ ዋነኛ አወዛጋቢ ጉዳይ የሆነው የዕድሜ ማጭበርበር

በአፍሪካ የስፖርት ውድድሮች ላይ ዋነኛ አወዛጋቢ ጉዳይ የሆነው የዕድሜ ማጭበርበር

ለዓመታት በአፍሪካ ስፖርት ላይ ጥቁር ጥላውን እንዳጠላ ነው። በቅርቡ በተካሄደው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ላይ የችግሩ ስፋት ታይቷል። የስፖርተኞች የዕድሜ ጉዳይ። ካሜሩን ባዘጋጀችው ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሳታፊ ከነበሩት አገራት መካከል አንዷ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ነበረች። ነገር ግን ከጨዋታው ጅማሬ በፊት ከውድድሩ እንድትሰረዝ ተደርጓል። ምክንያቱ ደግሞ ለውድድሩ ከተላኩት ተጫዋቾች መካከል 25ቱ ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በላይ መሆናቸውን የኤምአርአይ ምርመራ በማሳየቱ ነው። ከኮንጎ በተጨማሪ ቻድ እንዲሁ ተጫዋቾቿን ካሜሩን ከላከች በኋላ ከውድድሩ ተሰርዛለች። የካሜሮን እግር ኳስ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ኤቶ የኤምአርአይ ምርመራ እንዲደረግ ካዘዘ በኋላ፣ ቻድ ለውድድሩ ካቀረበቻቸው ተጫዋቾች መካከል 30ዎቹ የዕድሜ ገደቡን አልፈዋል። በመላው ዓለም የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖችን የሚያማክሩት…
Read More
ደቡብ ሱዳን ለዓለም የቅርጫት ኳስ ዋንጫ በመጀመሪያ ሙከራዋ በማለፍ ታሪክ ሰራች

ደቡብ ሱዳን ለዓለም የቅርጫት ኳስ ዋንጫ በመጀመሪያ ሙከራዋ በማለፍ ታሪክ ሰራች

የደቡብ ሱዳን የወንዶች የቅርጫት ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፈበት ማጣሪያው በዚህ ዓመት በሚካሄደው የዓለም ቅርጫት ኳስ ውድድር ለመሳተፍ ማለፍ በመቻሉ ታሪክ ሰራ። የደቡብ ሱዳን የቅርጫት ኳስ ቡድን በአፍሪካ የማጣሪያ ውድድር ውስጥ ሲሳተፍ የመጀመሪያው ቢሆንም ወደ ታላቁ ውድድር በመጀመሪያ ሙከራው በማለፉ በአፍሪካ የመጀመሪያው ሆኗል። ‘ብራይት ስታር’ እየተባለ የሚጠራው ቡድኑ በግብፅ አሌክሳንድሪያ በተደረገው ውድድር ሴኔጋልን 83 ለ 75 በመርታት በሚቀጥለው ነሐሴ በሚጀመረው እና ኢንዶኖኔዢያ፣ ጃፓን እና ፊሊፒንስ በጣምራ በሚያዘጋጁት የዓለም ቅርጫት ኳስ ዋንጫ እንደሚሳተፍ አረጋግጧል። በውድድሩ አፍሪካ በአምስት ብሔራዊ ብድን የምትወከል ሲሆን፣ አይቮሪ ኮስትም ቀደም ብላ ማለፏን አረጋግጣለች። እንደአውሮፓውያኑ የዘመን ስሌት በ2011 ከሱዳን ተለይታ ነጻ አገር ሆና የተመሠረተችው ደቡብ ሱዳን 11.5…
Read More
አንጋፋው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አንጋፋው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በኦሊምፒክ መድረክ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለመጀመሪያ ጊዜ በማውለብለብ ቀዳሚ የነበረው ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ ባደረበት ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል። የብስክሌት ስፖርተኛው ገረመው ደንቦባ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በትናንትናው ዕለት በ90 ዓመቱ ሕይወቱ ማለፉን ቤተሰቦቹ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ1956 ለመጀመሪያ ጊዜ በአውስትራሊያ ሜልቦርን ከተማ በተካሄደው የኦሊምፒክ ውድድር ስትካፈል ከተሳተፉ ብስክሌተኞች ገረመው ደንቦባ አንዱ ነበር። ብስክሌተኛ ገረመው ደንቦባ በበርካታ የብስክሌት ውድድሮች ተሳትፎ ከ26 በላይ ዋንጫዎችን እና ከ32 በላይ ሜዳሊያዎችን ተሸልሟል። አትሌቱ በስፖርቱ ዘርፍ ላበረከተው ጉልህ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚያዘጋጀው የኢቢሲ ስፖርት አዋርድ 4ኛው የኢቢሲ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ሽልማት የሕይወት ዘመን ተሸላሚ አትሌት ነበር። ገረመው ደንቦባ ታኅሣሥ 7 ቀን 1925 ዓ.ም በአዲስ…
Read More
ባሏን የገደለችው ዝነኛዋ አትሌት ጉዳይ

ባሏን የገደለችው ዝነኛዋ አትሌት ጉዳይ

አትሌት በሱ ሳዶ ከሁለት ወንድሞቿ እና ከሌሎች ሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በመሆን ባለቤቷን በመግደል ወንጀል ተከሳ ድርጊቱን መፈጸሟ በመረጋገጡ የእድሜ ልክ እስራት ተፈረደባት። በቅርበት የሚያውቋቸው የአዳማ አትሌቲክስ ክለብ አሰልጣኝ ሐብታሙ ግርማ ስለ ግድያው ሲናገሩ “እኔ በጣም ነው ያዘንኩት፤ በእርሱ ሞትም በጣም አዝኛለሁ። የእርሷም እስር ከሞት የማይተናነስ በመሆኑ እና አገሪቱም እንዲህ ዓይነት ሰው በማጣቷ በጣም ነው ያዘንኩት” ብለዋል። የአትሌት በሱ ሳዶ የቀድሞ አሰልጣኝ ስለ ሁኔታ ሲናገሩ የተፈጸመውን ወንጀል አምነው መቀበል እንዳዳገታቸው “እኔ አሁን ራሱ ይሄ ነገር እንዴት አንደተፈጠረ ሊገባኝ አልቻለም” ሲሉ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል። የመካከለኛ እና የረዥም ርቀት ሯጯ አትሌት በሱ ሳዶ እንዲሁም አብሯት የነበረው ወንድሟ ከባለቤቷ ግድያ ጋር በተያያዘ ጥፋተኛ ሆነው…
Read More
ተባባሪ መምህር

ተባባሪ መምህር

el_home_of_kids_academy education teaching assistant_teacher Addis Ababaበማንኛውም መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ላትየስራ ተግባራት እና ኃላፊነቶች፡- ለመልሶ ማስተማሪያ ወይም የመማር ሂደቱን ለማጠናከር ከትንንሽ የተማሪዎች ቡድን ጋር መስራት። የመማር ሂደቱን ለማሻሻል ከትንሽ የተማሪዎች ቡድን ጋር መስራት። ተማሪዎች እንዲያስተካክሉ፣ እንዲማሩ እና እንዲግባቡ፣ ሊኖሩ ስለሚችሉ የስነምግባር ጉዳዮች ለአስተማሪዎች ሪፖርት ያደርጋሉ።Quanitity Required: 1Minimum Years Of Experience: #0_yearsMaximum Years Of Experience: #1_yearsDeadline: October 6, 2022How To Apply: ሲቪ እና የትምህርት ማስረጃችሁን ኦርጅናልና ኮፒውን በመያዝ በአብነት አደባባይ፣ ዳርማር ጣቢያ አጠገብ በሚገኘው ኢ ኤል ሆም ኦፍ ኪድስ አካዳሚ በአካል በመቅረብ ማመልከት ወይም በኢሜል፡ amarechwolde2@gmail.com መላክ ትችላላችሁ።ማሳሰቢያ፡ ልምድ ያላቸው አመልካቾች ይበረታታሉ
Read More
አርት መምህር

አርት መምህር

el_home_of_kids_academy education teaching art_teacher Addis Ababaየባለሙያ ማረጋገጫ በአርትየስራ ተግባራት እና ኃላፊነቶች፡- በተማሪዎች የመማር ዓላማ መሰረት በሥነ ጥበብ እና በሥነ ጥበብ ታሪክ ላይ ትምህርቶችን ማቀድ። ተማሪዎች እንዲጠቀሙባቸው በክፍል ውስጥ የጥበብ ቁሳቁሶችን እና የጥበብ መሳሪያዎችን ማዘጋጀት::Quanitity Required: 1Minimum Years Of Experience: #0_yearsMaximum Years Of Experience: #1_yearsDeadline: October 6, 2022How To Apply: ሲቪ እና የትምህርት ማስረጃችሁን ኦርጅናልና ኮፒውን በመያዝ በአብነት አደባባይ፣ ዳርማር ጣቢያ አጠገብ በሚገኘው ኢ ኤል ሆም ኦፍ ኪድስ አካዳሚ በአካል በመቅረብ ማመልከት ወይም በኢሜል፡ amarechwolde2@gmail.com መላክ ትችላላችሁ።ማሳሰቢያ፡ ልምድ ያላቸው አመልካቾች ይበረታታሉ
Read More
የእንግሊዘኛ መምህር

የእንግሊዘኛ መምህር

el_home_of_kids_academy education teaching english_teacher Addis Ababaበእንግሊዝኛ የመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/ች ከአግባብ ያለው የሥራ ልምድ ጋርየስራ ተግባራት፡ የትምህርት ዕቅዶችን እና ቁሳቁሶችን ያዘጋጃሉ የተማሪውን ሂደት ይቆጣጠራሉ አስፈላጊ በሚሆንበት ጊዜ በተናጥል ያግዛሉ እና እውቀታቸውን እና አፈፃፀማቸውን በምድብ፣ በፈተና ይገመግማሉQuanitity Required: 1Minimum Years Of Experience: #0_yearsMaximum Years Of Experience: #1_yearsDeadline: October 6, 2022How To Apply: ሲቪ እና የትምህርት ማስረጃችሁን ኦርጅናልና ኮፒውን በመያዝ በአብነት አደባባይ፣ ዳርማር ጣቢያ አጠገብ በሚገኘው ኢ ኤል ሆም ኦፍ ኪድስ አካዳሚ በአካል በመቅረብ ማመልከት ወይም በኢሜል፡ amarechwolde2@gmail.com መላክ ትችላላችሁ።ማሳሰቢያ፡ ልምድ ያላቸው አመልካቾች ይበረታታሉ
Read More
ጸሐፊ

ጸሐፊ

el_home_of_kids_academy business secretarial_admin_and_clerical secretary Addis Ababaየቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና/ደረጃ IV/ እና ከዚያ በላይ በሴክሬታሪያል ሳይንስ፣ በአይቲ ወይም በተዛማጅ የትምህርት መስክየስራ ተግባራት እና ኃላፊነቶች፡- እንደ አስፈላጊነቱ ለርእ ሰመምህር ወይም ለሌላ ከፍተኛ ደረጃ አስተዳዳሪ አስተዳደራዊ ድጋፍ ይሰጣሉ። እንደ አስፈላጊነቱ መዝገቦችን ለማዘመን የኮምፒዩተር ዳታቤዝ ወይም የፋይል ስርዓት ይጠቀማሉ። ወደ ትምህርት ቤቱ ጎብኝዎችን ይቀበላሉ እና እንደ አስፈላጊነቱ በህንፃው ዙሪያ አቅጣጫዎችን ይሰጣሉ።Quanitity Required: 1Minimum Years Of Experience: #0_yearsMaximum Years Of Experience: #1_yearsDeadline: October 6, 2022How To Apply: ሲቪ እና የትምህርት ማስረጃችሁን ኦርጅናልና ኮፒውን በመያዝ በአብነት አደባባይ፣ ዳርማር ጣቢያ አጠገብ በሚገኘው ኢ ኤል ሆም ኦፍ ኪድስ አካዳሚ በአካል በመቅረብ ማመልከት ወይም በኢሜል፡ amarechwolde2@gmail.com መላክ ትችላላችሁ።ማሳሰቢያ፡ ልምድ…
Read More