SaudiArabia

​ሳዑዲ ዓረቢያ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ድንበር ሲያቋርጡ ማሰሯን ገለጸች

​ሳዑዲ ዓረቢያ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ድንበር ሲያቋርጡ ማሰሯን ገለጸች

አንደ ገልፍ ኒውስ ዘገባ የድንበር ጠባቂዎች ባለፉት አንድ ሳምንት ውስጥ 1,924 ሰዎች ሳዑዲ ዓረቢያ ለመግባት ሲሞክሩ በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዘዋል ብለዋል። ከእነዚህ ውስጥ 62 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን፣ 37 በመቶ የመን እና ቀሪዎቹ ደግሞ የሌሎች አገሮች ዜጎች ናቸው። በተጨማሪም 32 ሰዎች ከሀገር ለመውጣት ሲሞክሩ ተይዘዋል። ​በዘመቻው ወቅት ሕገ-ወጥ ስደተኞችን በትራንስፖርት፣ በመጠለያ ወይም በቅጥር ሥራ በማገዝ የተጠረጠሩ ተጨማሪ 31 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ​በአሁኑ ወቅት 30,236 የውጭ አገር ዜጎች የሕግ ሂደቶች እስኪጠናቀቁ ድረስ ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ ታስረው ይገኛሉ። ​የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕገ-ወጥ ስደተኞችን ማጓጓዝ፣ ማኖር ወይም በምንም መንገድ መርዳት እስከ 15 ዓመት በሚደርስ እስራት፣ እስከ 1 ሚሊዮን ሪያል በሚደርስ ቅጣት እና ጥቅም…
Read More
ኢትዮጵያ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎቿን ከውጭ ሀገራት መመለሷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎቿን ከውጭ ሀገራት መመለሷን ገለጸች

ከመስከረም ጀምሮ በሳዑዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ማቆያ ማዕከላት የሚገኙ ከ17 ሺሕ በላይ ዜጎች ወደ ሀገር መመለሳቸው ተገልጿል። በሳዑዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ማቆያ ማዕከላት የሚገኙ ዜጎችን ከ17 ሺሕ በላይ ዜጎችን ከመስከረም 05 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በተሰራ ሥራ መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴሩ በተለያዩ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል፡፡ "ከውጭ ግንኙነት ቁልፍ ሥራዎች አንዱ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ነው" ያለው ሚኒስቴሩ ፖሊሲውን በአግባቡ ለመተግበር በውጭ ሀገር የሚኖሩ ዜጎችን መብት ማስከበር፣ ለዜጎች ተገቢ የቆንስላ አገልግሎት መስጠት፣ በሄዱበት ሀገር ሕጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውና የሀገሩ መንግሥት ዜጎቻችን ሀገራቸውን እንዲለቁ ሲወስን መብታቸው፣ ክብራቸውና…
Read More
ሁለት ኢትዮጵያዊያን በግድያ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሁለት ኢትዮጵያዊያን በግድያ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ

በሳዑዲ አረቢያ ሁለት ኢትዮጵያውያን አንድ ህንዳዊ በመግደል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል። የሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት በቅርቡ በጂዳ ከተማ 'አንድ ህንዳዊ ዜጋ ላይ ተኩስ ከፍተው ገድለዋል' ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ዜጎችን በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ የጂዳ ግዛት ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፤ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ደንቦች በመጣስ በሕገ-ወጥ መንገድ በሚኖሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ክስ መመስረቱን አስታውቋል። በከተማዋ አቅራቢያ በሚገኝ ተራራማ አካባቢ ሕገ-ወጥ ዕፅ በመገበያያት ላይ በነበሩ ሰዎች መካከል በተፈጠረ ጠብና አለመግባባት ሳቢያ ህንዳዊው ግለሰብ በጥይት መመታቱን ገልፍ ኒውስ ዘግቧል፡፡ በዚህም በግጭቱ ወቅት ከተጠርጣሪዎቹ አንዱ ኢትዮጵያዊ በህንዳዊው ተጎጂ ላይ ተኩስ ከፍቶ ጉዳት እንዳደረሰበት የገለጸው ፖሊስ፤ በጥይት የተመታው ግለሰብ ወዲያውኑ በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታል ቢወሰድም፣…
Read More
በሃጅ ጉዞ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ከ1300 አለፈ

በሃጅ ጉዞ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ከ1300 አለፈ

በዘንድሮ የሃጅ ጉዞ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ከ1300 ተሻግሯል የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አምስቱ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውን ሳዑዲ አረቢያ ገልጻለች፡፡ በዘንድሮ የሃጅ ጉዞ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ከ1ሺህ 300 መሻገሩን ሳዑዲ አረቢያ አስታውቃለች። እስካሁን በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት የ10 ሀገራት ዜጎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፥ 658ቱ ግብጻውያን ናቸው ተብሏል። 150 ሺህ ሃጃጆችን የላከችው ፓኪስታን 58 ዜጎቿ ህይወታቸው ማለፉን ይፋ አድርጋለች። ከ240 ሺህ ኢንዶኔዥያውያን ሃጃጆች መካከልም 183ቱ መሞታቸውን የሀገሪቱ የሃይማኖቶች ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። የሱዳን፣ ሴኔጋል፣ ቱኒዚያ፣ ህንድ፣ ዮርዳኖስ፣ ማሌዥያና ኢራን ዜግነት ያላቸው ሃጃጆችም ህይወታቸው ማለፉን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። ከዚህ ውስጥ አምስቱ ኢትዮጵያዊን እንደሆኑ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ገልጿል፡፡ አብዛኛዎቹ ሟቾች ያለፈቃድ…
Read More
ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮያውያንን ወደ ሀገራቸው እመልሳለሁ ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ “በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለስ ሦስተኛ ምዕራፍ በሁለት ሳምንት ውስጥ ይጀምራል” ብለዋል። በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኘው ኢትዮያውያንን ለመመለስ የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመመለስ በተዘጋጀው ዕቅድ ላይ መክሯል። የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፤ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ በብሔራዊ ኮሚቴው ውስጥ የታቀፉት የፌዴራል ተቋማት እና የክልሎችን የጋራ ቅንጅት ይጠይቃል ብለዋል። ከወዲሁ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተሟላ ሁኔታ በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አምባሳደር ብርቱካን ተናግረዋል። አምባሳደር…
Read More
ኢትዮጵያ የዩንቨርሲቲ ምሩቃንን ወደ ውጪ ሀገራት ልትልክ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ የዩንቨርሲቲ ምሩቃንን ወደ ውጪ ሀገራት ልትልክ መሆኑን ገለጸች

የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን አሰልጥኖ ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለማሰማራት እንቅስቃሴ መጀመሩን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ምሩቃንን አሰልጥኖ ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለማሰማራት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጿል። ሚኒስቴሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 85 ሺህ ዜጎችን ወደ ውጭ ሀገር ለስራ ለመላክ አቅዶ 56 ሺህ ዜጎችን ወደ ውጪ ሀገራል ልኬያለሁ ብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ስድስት ሚሊዮን ዜጎች በስራ ፈላጊነት መመዘገባቸውንም ሚኒስቴሩ ገልጿል። የስራ እና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚል፤ በስራ እድል ፈጠራ፣ በቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና እንዲሁም በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት ላይ መስሪያ ቤታቸው ያከናወናቸውን ስራዎች ለፓርላማው አብራርተዋል። የሚኒስትሯን…
Read More
ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመላክ በምልመላ ላይ እንደሆነች ተገልጿል። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴቶች የጅምላ ምልመላ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል ። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች የሳውዲ አረቢያ የሰብዓዊ መብት አያያዟ ደካማ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴት ሠራተኞች የጅምላ ምልመላ አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡ አሁንም ቢሆን በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች በሳውዲ አረቢያ ከሠራተኛ ሕጎች የተገለሉ እና በዘመናዊ ባርነት ስርዓት ለጥቃት የተጋለጡ ናቸው ተብሏል፡፡ “ካፋላ” በተሰኘው ስርዓት አንድ ሠራተኛ በደል ቢደርስባት እና ከአሠሪዎቿ ብትሸሽ ፓስፖርቷን ጨምሮ የተለያዩ የሰነድ መረጃዎቿን እንድታጣ እንደሚደረግ እና ይህ ስርዓት አሁንም ለውጥ እንዳልተደረገበት ተገልጿል። ‹‹ሳውዲ አረቢያ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በዘፈቀደ በማሰር እና አሰቃቂ…
Read More
ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገር ልትልክ ነው በኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገራት በተለይም ወደ ሳውዲ አረቢያ ለሥራ ለመላክ በመንግሥት እቅድ መያዙ ተገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም በአማራ ክልል ኹሉም ዞኖች ሰሞኑን ወደ አረብ አገር ሄደው መስራት ለሚፈልጉ ወጣት ሴቶች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ኢትዮ ነጋሪ ሰምታለች፡፡ ለአብነትም በምስራቅ ጎጃም ዞን ሦስት የስልጠና ማዕከላት የተዘጋጁ ሲሆን፣ በሞጣ፣ ደብረ ማርቆስ እና ደጀን ከተሞች ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ሴቶች የቤት አያያዝና ሌሎች አስፈላጊ የሥራ ስልጠናዎች እንደሚሰጡኢትዮ ነጋሪ ከዞኑ መረጃ አግኝታለች፡፡ ስልጠናው ለ20 ቀን በመንግሥት በነጻ የሚሰጥ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፤ ከስልጠናው በኋላ ፈቃደኛ የሆኑ ሴቶች ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚያቀኑበት የዚህ…
Read More