15
May
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል ክፍያ ሰነድ አውጪ የሆነው ካቻ ዲጂታል ፋይናንሻል ሰርቪስ ከኢትዮጵያ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር አሽከርካሪዎች ካቻን በመጠቀም በቀላሉ የነዳጅ ክፍያን የሚከፍሉበትን አገልግሎት በትናንትናው እለት ይፋ አድርጓል። አገልግሎቱም ደንበኞች የካቻን መተግበሪያ በመጠቀም ፣ በ“Push USSD Notification” እንዲሁም በQR ኮድ ስካን በማድረግ በቀላሉ የነዳጅ ክፍያን መፈፀም የሚያስችል ሲሆን የካቻ ደንበኛ ያልሆነ ማንኛውምአሽከርካሪ መተግበሪያውን ከፕሌይስቶር ወይም አፕስቶር በማውረድ ከማንኛውም ባንክ ወደ ካቻ ገንዘብ በማስተላለፍ ወዲያውኑ ክፍያ መፈፀም እንደሚያስችል ተገልጿል። "የዛሬው ምርቃት ካቻ ለማህበረሰባችን ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ፉይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ለሚያደርገው ጉዞ አንድ እርምጃ የሚያግዘን ነው"ያሉት የካቻ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብርሀም ጥላሁን "በቀጣይም ካቻ በአሽከርካሪዎች ላይ ያለውን የፋይናንስ ጫና…