AddisAbaba

አረብ ኢምሬት የሰዎች ዝውውር ወንጀል ተጠርጣሪዎችን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጠች

አረብ ኢምሬት የሰዎች ዝውውር ወንጀል ተጠርጣሪዎችን ለኢትዮጵያ አሳልፋ ሰጠች

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ዱባይ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በኢትዮጵያውያን ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ የነበሩ ዳውድ ተፈሪ እና ደስታ ተገኝ የተባሉ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ የማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም 105 ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ዱባይ በመውሰድና ከ188 ሚሊየን ብር በላይ ከተጎጂዎች በመሰብሰብ፣ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲፈጽሙ የቆዩ በመሆናቸው ከዱባይ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ሥር ውለው ለኢትዮጵያ ተላልፈው እንዲሰጡ ተደርጓል ብሏል። ተጠርጣሪዎቹ ዱባይ ተቀምጠው ሀገር ውስጥ ባሉ ተባባሪዎቻቸው አማካኝነት ወጣቶችን በመመልመል ወደ ዱባይ በመላክ፣ በተዘጋጀ የማገቻ ቦታ በማቆየት፣ በተለይ በሴቶች ላይ ጥቃት በማድረስና በማሰቃየት ከፍተኛ ወንጀል ሲፈጽሙ የቆዩ መሆናቸው ተረጋግጧል። ፌደራል ፖሊስም ጉዳዩን ሲያጣራ ቆይቶ…
Read More
ኢትዮጵያ ለ15 ሀገራት ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ እንደማትሰጥ አስታወቀች

ኢትዮጵያ ለ15 ሀገራት ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ እንደማትሰጥ አስታወቀች

የኢትዮጵያ ዜግነት እና ኢምግሬሽን እንዳስታወቀው ከ15 ሀገራት ዜግነት ያላቸው መንገደኞች የመዳረሻ ቪዛ እንደማያገኙ ገልጿል። ከኤርትራ፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶሪያ፣ አፍጋኒስታን፣ ኩባ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ፣ የመን እና የኢራን ዜጎች የመዳረሻ ቪዛ ወይም ቪዛ ኦን አራይቫል የማይሰጣቸው ሀገራት ናቸው። የኬንያ እና ጅቡቲ ዜጎች ግን ያለ ቪዛ ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ተፈቅዶላቸዋል ተብሏል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተቋሙን ዓመታዊ አፈጻጸም አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ከ1 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ቪዛ መሰጠቱን ተናግረዋል ። ተቋሙ በአንድ ዓመት ውስጥ ከአገልግሎት ፈላጊዎች 42 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡም ተገልጿል። በበጀት ዓመት 7 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሰዎች በአየር መንገዶች እና…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 7ኛ ስብሰባው፣ የተለያዩ የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን አቅርቦ ማጽደቁን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠርና ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ያለመ አዳዲስና ወሳኝ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቋል። ኮሚቴው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መወሰኑንም ገልጿል። እስካሁን ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ ተጥሎ የነበረው የ24 በመቶ ቀጥተኛ የብድር ዕድገት ገደብ ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል። በባንኮች ላይ የብድር ገደብ ውሳኔ ተጥሎ የነበረው ኢኮኖሚው በወለድ ምጣኔ ላይ ወደተመሠረተ የገንዘብ ፖሊሲ ሥርዓት እስኪሸጋገር እንደነበር…
Read More
የሁለተኛ ድግሪ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጀ

የሁለተኛ ድግሪ ትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥ የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጀ

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የከፍተኛ ትምህርት ማስረጃ አሰጣጥንና የደረጃ ግምገማ ሂደትን ለማሻሻል ያስችላል የተባለውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ ለህዝብ አስተያየት ክፍት አድርጓል። ባለስልጣኑ "የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 990/2016" ላይ ማሻሻያ ለማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት ጥሪ አቅርቧል። ተቋሙ እንዳስታወቀው ይህ መመሪያ ያስፈለገው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የትምህርት ማስረጃዎችን የማረጋገጥ ሂደት ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልጽ ለማድረግ በሚል ነው። በተለይም በደረጃ ግምገማ እና በማስረጃ ማረጋገጫ ሂደት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ታልሞ መዘጋጀቱም ተገልጿል። ይህ መመሪያ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የመንግስትም ሆነ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተምረው ከ2010 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ለተመረቁ…
Read More
የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ነጋዴዎችና ላኪዎች የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ታዳጊ ሀገራትን ተጠቃሚ የሚያደርገውን የንግድ ሥርዓት በተሻለ ሁኔታ ተጠቅመው ወደ ዩኬ ገበያ የመግባት ዕድላቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ ቀረበ። ይህ ጥሪ በአዲስ አበባ በተካሄደው የሥልጠና መድረክ ላይ የተላለፈ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ላኪዎች የዕድሉን፣ የመስፈርቶቹንና የተግባራዊ ሂደቶቹን ግንዛቤ እንዲያሳድጉ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከዩኬ የንግድና ልማት መሥሪያ ቤት፣ ከብሪታንያ ኤምባሲና ከኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ የዩኬ ገበያ ለመግባት የሚያስፈልጉ የጥራት ደረጃዎችና የቁጥጥር መስፈርቶች ተብራርተዋል። አምባሳደር ብሩክ መኮንን እንደገለጹት፣ ቡና፣ የግብርና ምርቶችና ጨርቃጨርቅ በዚህ ሥርዓት ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ የወጪ ንግድ ዘርፎች ናቸው። ሆኖም፣ የቀረጥ ቅናሹ ብቻውን…
Read More
በትግራይ ክልል ታዳጊዎች በሀይል ለውትድርና እየተመለመሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

በትግራይ ክልል ታዳጊዎች በሀይል ለውትድርና እየተመለመሉ መሆኑን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እንዳስታወቀው ከሰኔ 17 ቀን 2018 ጀምሮ ደግሞ የግዳጅ ውትድርና ህግ ወጥቶለት ስራ ላይ መዋሉን ገልጿል። ይህ አዋጅ የዜጎችን ሰብአዊ መብቶችን የሚጥስ በመሆኑ እንዲቆም ኮሚሽኑ አሳስቧል፡፡ በትግራይ ክልል የግዳጅ ውትድርና ሰነድ ከመውጣቱ  አስቀድሞ በተለያዩ አካባቢዎች ወጣቶችን በተለይም ሕጻናትን፣ ተፈናቃዮችን፣ የአእምሮ ጤና ሕሙማንን፣ እንዲሁም ከስደተኛ ካምፖችና ከጸበል ሥፍራዎች ጭምር በግዳጅ በማሰባሰብ ወደ ወታደራዊ ሥልጠና ካምፖች የማስገባት ተግባር ሲፈጸም እንደነበር ኢሰመኮ ተናግሯል፡፡ ኮሚሽኑ የግዳጅ ውትድርና ሰነዱ ከወጣ በኋላም ይህ ተግባር ይበልጥ ተጠናክሮ ቀጥሎ የአብነት ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ከአብያተ ክርስትያናት፣ እንዲሁም በርካታ ሌሎች ሰዎችን ከገበያ ስፍራ፣ ከወጣቶች ማዘውተሪያ ማዕከላት እና ቤት ለቤት በሚደረግ አሰሳ በማፈስ ወደ ወታደራዊ ተግባር እንዲሰማሩ መደረጉን…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ የብድር ስምምነት ዙሪያ እንድትጠነቀቅ የዓለም ባንክ አሳሰበ

ኢትዮጵያ በአዲስ የብድር ስምምነት ዙሪያ እንድትጠነቀቅ የዓለም ባንክ አሳሰበ

ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር ያፀደቀው የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ከአዳዲስ የብድር ጫና እንድትቆጠብ አስጠንቅቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከእዳ ጫና እንድትላቀቅ በምትፈጽማቸው አዳዲስ የብድር ስምምነቶች ዙሪያ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ልትወስድ እንደሚገባ አስታውቋል። ተቋሙ አምስተኛውን የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ግምገማ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ተጨማሪ 464 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለኢትዮጵያ አጽድቋል። የተቋሙ የበጀት ድጋፍ ከሁለት አመት በፊት ያፀደቀውና ለአራት አመት በሂደት የሚለቀቅ በሚል የፈቀደው የ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ብድር አካል ነው፡፡ የአይኤምኤፍ የስራ አመራር ቦርድ ያፀደቀው የ464 ሚሊዮን ዶላር ብድር እስካሁን በአራት ዙር ከተለቀቀው ሁሉ የላቀ ሲሆን ለወደፊቱ ከሚለቀቀው ብድር ታሳቢ የሚደረግ የ200 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ ታክሎበታል። ጭማሪ ገንዘቡ…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተያዘው በጀት ዓመት 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል። የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለጹት፣ የተገኘው ትርፍ ባንኩ ባለፉት ጊዜያት ካጋጥሙት የህልውና አደጋ መውጣቱን ያሳያል ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ባንኩ ከስድስት ዓመታት በፊት ከነበረበት ችግር ወጥቶ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ደረጃ ቀዳሚ ከሚባሉ ጠንካራ ባንኮች ተርታ መሰለፉንም ተናግረዋል። ባንኩ ለደረሰበት ከፍተኛ የትርፍ መጠን በዋናነት ለግል ዘርፉ የሰጠው ትኩረት፣ የተበላሸ ብድር መጠን መቀነሱ እና የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት መስፋፋትን በምክንያትነት አንስተዋል። ባንኩ እየተጠናቀቀ ባለው የዘንድሮው በጀት ዓመት 648 ቢሊዮን ብር አዲስ ብድር እንደሰጠም ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል። ከተሰጠው ብድር ውስጥም 90 በመቶ የሚሆነውን ወይም 588 ቢሊዮን ብር ለግል ዘርፍ መቅረቡም ተገልጿል።…
Read More
በህገወጥ የቡና አዘዋዋሪዎች ላይ የ50 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ቅጣት ተጣለ

በህገወጥ የቡና አዘዋዋሪዎች ላይ የ50 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ቅጣት ተጣለ

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀገሪቱ ዋነኛ የወጪ ንግድ ገቢ ምንጭ በሆነው የቡና ምርት ላይ የሚፈጸመውን ህገ-ወጥ ዝውውር (ኮንትሮባንድ) ለመግታት፣ ከተባባሪ አካላት ጋር በመቀናጀት ጥብቅ የሆኑ የቁጥጥርና የቅጣት እርምጃዎችን መተግበር መጀመሩን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶ/ር ሰፊሳ አባቡ እንደተናገሩት ህገ-ወጥ የቡና ንግድ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በእጅጉ እየጎዳ በመሆኑ፣ ድርጊቱን ለመከላከል አዲስ የክትትል ስትራቴጂ ተቀርጾ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል። በዚህም መሠረት ባለስልጣኑ ህገ-ወጥ የቡና ዝውውርን ለማስቆም ከፌዴራልና ክልል ፖሊስ፣ ከጉምሩክ ባለስልጣን እና ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር የጋራ ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየተሰራ መሆኑንም ኋላፊው አክለዋል። በመሆኑም ያለ ህጋዊ ፈቃድና ሰነድ ሲንቀሳቀስ የተገኘ ማንኛውም የቡና ምርት ሙሉ በሙሉ በመንግስት ይወረሳል ተብሏል። በህገ-ወጥ…
Read More
ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በካርበን ግብይት ውስጥ እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በካርበን ግብይት ውስጥ እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላንና ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ የተበታተነውን የካርበን ግብይት በአንድ የሕግ ማዕቀፍ ለማስተዳደር እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ጅምር ስራዎችን ለማጠናከር እንደሚረዳ በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብርት ለውጥ ተጋላጭ መሆኗን ያስታወሰው የካርበን ረቂቅ አዋጅ ለአማቂ ጋዝ ልቀት ቅነሳ ደጋፍ ማድረግ እና በአየር ንብርት ለውጥ ላይ አደገኛ ጣልቃ ገብነትን ማስቀረት "የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው" ብሏል። በአስር ክፍል እና በ44 ገጽ የተዘጋጀው ይህ የካርበን ግብይት ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በአለም አቀፍ ደረጃ የተፈራረመችውን ስምምነት ለመተግበርም እንደሚረዳ በአላማዎቹ ስር ተጠቅሷል። ረቂቁ…
Read More