AddisAbaba

ኢትዮጵያ የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ በፋዊ ጥያቄ አቀረበች

ኢትዮጵያ የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ በፋዊ ጥያቄ አቀረበች

​ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2028 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) ውድድር ለማስተናገድ ይፋዊ የጨረታ ጥያቄዋን ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ማቅረቧን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ሀገሪቱ ውድድሩን ለመጨረሻ ጊዜ ያዘጋጀችው በ1976 እንደመሆኑ መጠን፣ ጥያቄው ከተቀባይነት ካገኘ ከ50 ዓመታት በላይ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ትልቁን አህጉራዊ መድረክ ዳግም ይመልሳል። ​የ2028ቱ ውድድር ከአፍሪካ ዋንጫ የተለመደ ባለሁለት ዓመት ዑደት ተለውጦ በየአራት ዓመቱ መካሄድ የሚጀምርበት የመጀመሪያው ውድድር ይሆናል። 130 ሚሊዮን ሕዝብና የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ዝግጁነቷን ብታረጋግጥም፣ በባህር ዳር እና በመዲናዋ የሚከናወኑ የስቴዲየም ግንባታዎች እንዲሁም የጸጥታ ስጋቶች በዝግጅት ሂደቱ ላይ የሚጠበቁ ተፎካካሪ ተደራራቢ ፈተናዎች ናቸው። ​በፊፋ ደረጃ 143ኛ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ እ.ኤ.አ. በ2027 ጎረቤቶቿ ኬንያ፣…
Read More
በኢትዮጵያ ቻይንኛ ቋንቋን ለሀይስኩል ተማሪዎች መስጠት ሊጀመር ነው

በኢትዮጵያ ቻይንኛ ቋንቋን ለሀይስኩል ተማሪዎች መስጠት ሊጀመር ነው

ከቻይና መንግስት ጋር ባለው ግንኙነት መሰረት መስከረም ላይ በሚጀምረው የ2019 ትምህርት ዘመን በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የቻይንኛ ቋንቋ እንዲሰጥ ለማድረግ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ መሆኑን የትምህርት ሚንስቴር ገልጿል። በእነዚህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ቻይንኛን የሚያስተምሩ መምህራን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉም ተብላል። በትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ የትምህርት ፕሮግራሞችና ጥራት ማሻሻል መሪ አስራአስፈፃሚ ዶ/ር ዮሀንስ ወጋሶ የአዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያላቸውና በመለያ ፈተና አልፈው የሚገቡ መሆናቸውን አንስተዋል። እነዚህ ተማሪዎች በአለም አቀፍ ደረጃ ውጤታማና ስኬታማ እንዲሆኑ ለማድረግም የተለያዩ የውጪ ሀገር ቋንቋዎችን እንዲማሩ እንደሚደረግ ለአሀዱ ሬዲዮ ተናግረዋል። በተለይም ደግሞ ተማሪዎች የከፍተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በውጪ ሀገር የመከታተል እድል ያላቸው በመሆኑ ለዛ እንዲጠቅማቸው…
Read More
565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ወደ ዩንቨርስቲ አላስገቡም ተባለ

565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ወደ ዩንቨርስቲ አላስገቡም ተባለ

በዘንድሮው ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 565 ያህሉ አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸው ተገልጻል። ዘንድሮ በ2018 ብሔራዊ ፈተና የተመዘገበው ተማሪ ቁጥር 563,960 ሲሆን  550,210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል። ከተፈተኑት ውስጥም 12 በመቶ ወይም 70 ሺህ 544 ተማሪዎች ብቻ ወደ ዩንቨርስቲ የሚያስገባቸውን ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል። ከተፈጥሮ ሳይንስ 16.6 በመቶ እንዲሁም ከማህበራዊ ሳንይስ 8.3 በመቶ ያህሉ ማለፋቸውን የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ተናግረዋል። አዲስ አበባ ካስፈትናቸው ተማሪዎች ውስጥ 32.3 በመቶዎቹ ሲያልፉ፣ ሀረሪ 22.67%፣ አፋር 15.6%፣ አማራ 15.56%፣ ድሬዳዋ 11.29፣፣ ትግራይ 11.2%፣ ኦሮሚያ 10.5 በመቶ አሳልፈዋል። ባለፉት ዓመታት ዋነኛ የግጭት እና ጦርነት ቀጠና በሆኑት በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ትግራይ ክልል ያለፉ ተማሪዎችን ስንመለከትም በኦሮሚያ…
Read More
ኢትዮጵያ በኬንያ በሚገነባው የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ድርሻ መግዛት ተፈልጋለች ተባለ

ኢትዮጵያ በኬንያ በሚገነባው የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ድርሻ መግዛት ተፈልጋለች ተባለ

የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊኒየር ናይጀሪያዊው አሊኮ ዳንጎቴ በኬንያ ላሙ አካባቢ ለመገንባት ላቀዱትና በቀን 700,000 በርመል ነዳጅ የማጣራት አቅም የሚኖረው ግዙፍ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ማቀዱ ይታወሳል። ይህ ፕሮጀክት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የ30 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ እንዲገዙ ጥያቄ የቀረበ ሲሆን ኢትዮጵያ የተወሰነ ድርሻ የመግዛት ፍላጎት እንዳላት ተገልጿል። የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የኢኮኖሚ አማካሪ ዴቪድ ንዲ በናይሮቢ በተካሄደ የካፒታል ማርኬት መድረክ ላይ ይህንን የኢትዮጵያ ፍላጎት ይፋ ማድረጋቸውን እንደሆነ ብሉምበርግ ዘግቧል። አማካሪው ከዚህ ግዙፍ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የ30 በመቶ የባለቤትነት ድርሻ መቅረቡን ገልጸዋል። አማካሪው አክለውም፥ ኬንያ 500 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣውን የ10 በመቶ ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት ማሳየቷንና ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳም በፕሮጀክቱ…
Read More
የኬንያው አጋካን ዩንቨርስቲ ሆስፒታል ከኢትዮጵያ አቻ ተቋማት ጋር መስራት እንደሚፈልግ ገለጸ

የኬንያው አጋካን ዩንቨርስቲ ሆስፒታል ከኢትዮጵያ አቻ ተቋማት ጋር መስራት እንደሚፈልግ ገለጸ

መሰረቱን እስያ ያደረገው እና ኬንያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስክ የተሰማራው አጋካን ዩንቨርስቲ ሆስፒታል በኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳለው ገልጿል። ሆስፒታሉ በኢትዮጵያ ያሉ የጤና ኢንቨስትመንት አማራጮችን ለመጠቀም ከዩንቨርሲቲዎች እና የጤና ተቋማት ጋር ትብብር በማድረግ ላይ እንደሆነ አስታውቋል። የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ ራሺድ ካላኒ ዛሬ ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ያለውን የጤና ፍላጎት መጠቀም እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። እንደ ስራ አስኪያጁ ገለጻ ከሆነ አጋካን ዩንቨርስቲ ሆስፒታል በትብብር መስራት ከሚፈልጉ የኢትዮጵያ ጤና እና ኢንቨስትመንት ተቋማት ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ስምቶችን በማድረግ ይገኛል። ለአብነትም በጤና ባለሙያዎች ስልጠና፣ በልምድ ልውውጥ ፣ በጋራ ጥናትና ምርምር ስራዎች ከኢትዮጵያ አቻ ተቋማት ጋር የመስራት…
Read More
የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ባለበት እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደረሰ

የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ባለበት እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደረሰ

ከአንድ ወር በላይ የቆየው የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች እየተወያዩባቸው ካሉ ጉዳዮች መካከል የሰንደቅ አላማ ጉዳይ አንዱ ሲሆን አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ቀለም ባለበት እንዲቀጥል ነገር ግን መሀሉ ላይ ያለው አርማ እንዲቀየር ከስምምነት ላይ ተደርሷል። ከ8ቱም ቡድኖች በተመረጡ አጠናቃሪዎች የተዋቀረው አዘጋጅ ቡድን እያንዳንዳቸው 500 ሰዎችን ከያዙ 8 ቡድኖች ተቀብሎ ያጣጣማቸውን፣ ድግግሞሽ እንዳይኖር ያስወገደላቸውን የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች አዘጋጅቶ የ8ቱንም ቡድኖች ምክረ ሀሳቦች የያዘ ቃለጉባዔ ለ8ቱም ቡድኖች አቅርቧል። ተመካካካሪዎች በተለያዩ ቡድኖች ተደራጅተው ሀሳብ ከማመንጨት እስከ በሀሳቦቹ መከራከር ድረስ ከመከሩባቸው ስምንት አጀንዳዎች መካከል የሀገር ግንባታ አጀንዳ አንዱ ሲሆን፣ በዚሁ አጀንዳ በዛሬው ቃለጉባዔ ከተነሱት ምክሮች መካከል የቋንቋ ጉዳዮችተጠቃሽ ናቸው። የቋንቋ ጉዳይን በተመለከተ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ ይኑራት?…
Read More
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርትን ለመገንባት ከስምንት በላይ ሀገራት እየተፎካከሩ ነው ተባለ

የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርትን ለመገንባት ከስምንት በላይ ሀገራት እየተፎካከሩ ነው ተባለ

ኢትዮጵያ የቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት መንገደኞችን ከማስተናገድ አንጻር እቅሙ ተዳክሟል በሚል ምክንያት በ12 ቢሊዮን ዶላር አዲስ ኤርፖርት ለመገንባት ማቀዷ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በ12 ቢሊዮን ዶላር ለመገንባት የዲዛይን ስራው ተጠናቆ የተቋራጭ ድርጅቶች መረጣ በመካሄድ ላይ ይገኛል። በዚህ ኤርፖርት ግንባታ የመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ተቋራጮች እንዲወዳደሩ ዓለም አቀፍ የመጀመሪያ ዙሪ ማስታወቂያ መውጣቱን ተከትሎ የአሜሪካ ፣ አውሮፓ ፣ እስያ እና ሌሎችም ሀገራት ፍላጎታቸውን አሳውቀዋል። በዚህም መሰረት የቻይና የግንባታ ተቋማት በብዛት ፍላጎታቸውን እንዳሳዩ ተገልጿል። በቀረበው የእጩዎች ዝርዝር መሰረት ከወጡት አራት ዋና ዋና የሥራ ክፍሎች  ውስጥ የቻይና ተቋማት በተናጠልና በቅይጥ በብዛት ተካተዋል። የቻይና ኮሙኒኬሽንስ ኮንስትራክሽን ኩባንያ (CCCC)፣​ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን…
Read More
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የምክክር ሂደቱ ላይ የተነሱበትን ቅሬታዎች ውድቅ አደረገ

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን የምክክር ሂደቱ ላይ የተነሱበትን ቅሬታዎች ውድቅ አደረገ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የምክክር ሂደቱን «ተዓማኒነት»፣ «አካታችነት»፣ «ገለልተኝነት» እና «ፍትሐዊነት» ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ተደጋጋሚና የተደራጁ ጥፋቶች ተፈጽመዋል በሚል ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምላሽ ሰጥቷል። ኮሚሽኑ አብን ነሀሴ 08 ቀን 2019 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ በሰጠው ምላሽ፣ ፓርቲው ሂደቱ «አካታች» እና «አሳታፊ» አይደለም በሚል ያቀረበውን መግለጫ መመርመሩንና ማጣራቱን ገልጾ፣ የፓርቲውን ድምዳሜ እንደማይቀበለው ይፋ አድርጓል። ፓርቲው ወደ ምክክሩ የገባው ችግሮች በኃይል ሳይሆን በውይይት፣ በጫና ሳይሆን በመደማመጥ፣ በአንድ ወገን የበላይነት ሳይሆን በጋራ መግባባት፣ እንዲሁም ሁሉም አሸናፊ በሚሆንበት ሰጥቶ የመቀበል መርህ እንደነበር በመግለጫው አስታውሷል። ሆኖም በሂደቱ ውስጥ ከተራ የአሰራር ግድፈት የተለየ ሁኔታ መመልከቱን የዘረዘረው አብን፣ ሂደቱን ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ተዓማኒነትን፣ አካታችነትንና ፍትሐዊነትን…
Read More
ባህርዳር ስታዲየም የካፍ እውቅና ተሰጠው

ባህርዳር ስታዲየም የካፍ እውቅና ተሰጠው

ባሕርዳር ስታዲየም ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ተፈቅዶለታል። የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስፈርቶችን በማሟላት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ፈቃድ አግኝቷል። ኢትዮጵያ የካፍ እና ፊፋ እውቅና ያለው ስታዲየም ባለቤት ባለመሆኗ ዋልያዎቹን ጨምሮ ክለቦች በውሰት ሜዳዎች ሲጫወቱ ቆይተዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም መስፈርቶችን ባለማሟላቱ ዓለምአቀፍ ጨዋታዎችን እንዳያደርግ አግዶት ቆይቷል። በዚህ ምክንያት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሌሎች ሀገራት እንዲጫወት ተገድዶ ቆይቷል። ካፍ የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም የዓለም አቀፍ ስታዲዬም ማሟላት የሚገባውን መስፈርት እንዲያሟላ አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወሳል። ባለፉት ዓመታት ስታዲዬሙ የካፍ መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ ግንባታ ሲካሄድለት ቆይቶ አሁን ላይ መስፈርቶችን በማሟላቱ ማረጋገጫ ተሰጥቶታል ተብሏል። ኢትዮጵያ የካፍ…
Read More
ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት እንድትመራ ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በፕሬዝዳንት እንድትመራ ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በፕሬዚዳንት እንድትመራ በሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ተመካካሪዎች መግባባት መደረሳቸው ተሰምቷል። ይሁንና ፕሬዚዳንቱ በሕዝብ ይመረጥ ወይስ በፓርላማ በሚለው ጉዳይ ተመካካሪዎች ስምምነት ላይ አለመድረሳቸው ተገልጿል። ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ቀርቶ በፕሬዚዳንት እንድትመራ፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ሥርዓት አጀንዳ ላይ የ500 ቡድን ተመካካሪዎች ሙሉ በሙሉ በምክረ-ሐሳብ ደረጃ መግባባት ላይ ደርሰዋል ተብሏል። በዚሁ አጀንዳ ላይ ተወያይ የነበሩ ተመካካሪዎች ለሪፖርተር በሰጡት አስተያየት፣ በቀረቡት አብዛኞቹ ምክረሐሳቦች መግባባት ላይ መደረሱን ሆኖም ያላግባቡና ወደ ቀጣይ የተሻገሩ ጉዳዮች መኖራቸውንም ገልጸዋል። በዚህም የ500 ቡድን ተመካካሪዎች የአገሪቱ አስተዳደር ሥርዓት ፓርላሜንታሪ ሆኖ እንዲቀጥል፣ የአገሪቱ መሪ ፕሬዚዳንት እንዲሆን፣ አዲሱ ተመራጭ ፕሬዚዳንትም የጠቅላይ ሚኒስትሩና የፕሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባርን…
Read More