12
May
ተቋሙ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽመዋል ያላቸውን 1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ እርምጃመውሰዱን አስታውቋል። እርምጃ ከተወሰደባቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች መካከል 16 ሲሰናበቱ፤ 721 የደሞዝ ቅጣት የተቀጡ እንዲሁም 402 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ናቸው፡፡ አገልግሎቱ በ1 ሺህ 139 ሠራተኞች ላይ ከወሰዳቸው አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል 103 ሠራተኞች ላይ በደንበኞች የቀረበን ጥቆማ በመመርመር የወሰደው ሲሆን ቀሪ 1 ሺህ 36ቱ ተቋሙ በራሱ ግኝት አጣርቶ የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት አገልግሎቱ በሙስና መጠቆሚያ ዘመናዊ መተግበሪያ (Corruption Reporting App) እና በሌሎች አማራጮች ከደንበኞቹ የደረሱትን 427 ጥቆማዎችን መርምሮ በ103 ኃላፊዎችና ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎችን ወስጃለሁ ብሏል፡፡ በደንበኞቹ በቀረቡት ጥቆማዎች መሰረት 14 የፅሁፍ፣ 80 የደሞዝ ቅጣት፣ 2 ከቦታ የማንሳትና 7 ስንብት በድምሩ 103…