ዜና

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አለም አቀፍ ሹመት አገኙ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አለም አቀፍ ሹመት አገኙ

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት እና አንጋፋ ዲፕሎማት የሆኑት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት  አዲስ ሹመት ማግኘታቸው ተገልጿል፡፡ ሹመቱን የተመድ ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ እንደሰጡ ቢሮው በጉዳዩ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። ፕሬዝደንቷ የተመደቡት በምእራብ አፍሪካና ሳህል ቢሮ ውስጥ ገለልተኛ ስትራቴጂያዊ ግምገማ እንዲያደርጉ ሲሆን፣ ዋና ተግባራቸውም ተቋሙ ለአካባቢው ቀውሶች በሚሰጠው ዘገምተኛ ምላሽ ሳቢያ የሚነሱበትን ትችቶችና የአሰራር ክፍተቶችን መመርመር ነው።ወይዘሮ ሳህለወርቅ ከሀምሌ ወር ጀምሮ አዲሱን ሹመት ተቀብለው ስራ እንደሚጀምሩ ተገልጿል፡፡ ወይዘሮ ሳህለወርቅ ስራቸውን ከመጀመራቸው በፊት በመጀመሪያ ወደ ኒውዮርክ በማቅናት ከፀጥታው ምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ይቀበላሉ የተባለ ሲሆን፣ በመቀጠልም የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ወደሚገኝበት ሴኔጋል ዳካር በመጓዝ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ይወያያሉ።ለቀድሞዋ ፕሬዝደንት ይህ…
Read More
ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በካርበን ግብይት ውስጥ እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት በካርበን ግብይት ውስጥ እንዲሳተፉ የሚፈቅድ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላንና ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በካርበን ገበያ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ የተበታተነውን የካርበን ግብይት በአንድ የሕግ ማዕቀፍ ለማስተዳደር እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እየተከናወኑ ያሉ ጅምር ስራዎችን ለማጠናከር እንደሚረዳ በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብርት ለውጥ ተጋላጭ መሆኗን ያስታወሰው የካርበን ረቂቅ አዋጅ ለአማቂ ጋዝ ልቀት ቅነሳ ደጋፍ ማድረግ እና በአየር ንብርት ለውጥ ላይ አደገኛ ጣልቃ ገብነትን ማስቀረት "የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ነው" ብሏል። በአስር ክፍል እና በ44 ገጽ የተዘጋጀው ይህ የካርበን ግብይት ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በአለም አቀፍ ደረጃ የተፈራረመችውን ስምምነት ለመተግበርም እንደሚረዳ በአላማዎቹ ስር ተጠቅሷል። ረቂቁ…
Read More
ለአዲሰ አበባ ከተማ ዓመታዊ በጀት 502 ቢሊዮን ብር ተመደበ

ለአዲሰ አበባ ከተማ ዓመታዊ በጀት 502 ቢሊዮን ብር ተመደበ

ከተመደበው በጀት ውስጥ ትልቁን ድርሻ የያዘው ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ በሚል የተመደበው ነው ተብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ሰኔ 12፣ 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው፤ የከተማዋን የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በዚህም መሰረት ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚጀምረው የ2019 በጀት ዓመት የአዲስ አበባ ከተማ በጀት 502 ነጥብ 27 ቢሊዮን ብር ሆኖ ወደ ምክር ቤት እንዲመራ መመርያ ሰጥቷል ። ረቂቅ በጀቱ የከተማ አስተዳደሩን የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣ድህነትን ለመቀነስ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማረጋገጥ ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ ተዘርዝሯል። በተጨማሪም የከተማውን ነዋሪ የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት አቅርቦት ለማሳደግ በተለይም  የስራ እድል ፈጠራን ለሚያበረታቱ የመሰረተ…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የ1 ነጥብ ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ዓለም ባንክ ከአንድ ወር በኋላ ለኢትዮጵያ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በጀት ድጋፍ ሊያጸድቅ መሆኑን ገልጿል። አንድ የባንኩ ከፍተኛ ባለሙያ ሲናገሩ አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የገንዘብ ሚኒስቴር ከሳምንት በፊት የ2019 ዓ.ም የበጀት ረቂቀን ለምክር ቤቱ ባቀረበበት ወቅት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ መሆኑን ገልፆ የበጀት ጉድለቱ ከውጭ እርዳታ እና ሀገር ውስጥ በሚገኝባቸው ገቢ ይሸፈናል ማለቱ ይታወሳል። በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ የግሉ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ብስራት ተሾመ እንደገለጹት ከሆነ ባንኩ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚውል የአንድ ጊዜ የበጀት ድጋፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ተናግረዋል። ባለሙያው ይህን ያሉት ትናንት ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር ባዘጋጁት የውይይት መድረክ…
Read More
ጁንቱ ቴክኖሎጂ የ“ቼሪ” ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ ጀመረ

ጁንቱ ቴክኖሎጂ የ“ቼሪ” ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ ጀመረ

“ጁንቱ ቴክኖሎጂስ ግሩፕ” የ“ቼሪ” አውቶሞቢል ኩባንያ (Chery Automobile) ምርቶችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ መጀመሩን አስታወቀ፡፡  ድርጅቱ “ኦሞዳ” (OMODA E5) እና “ጃይኮ” (JAECOO J5) የተሰኙትንና የ“ቼሪ” ምርቶች የሆኑትን ሁለት የኤሌክትሪክ መኪና ሞዴሎችን ለኢትዮጵያ ገበያ በማቅረብ የዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ወኪል አቅራቢነቱን ማስፋፋቱን ገልጿል፡፡   ድርጅቱ ስራውን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታወቀ አገልግሎት፣ በላቀ ቴክኖሎጂ እና በረጅም ጊዜ የገበያ ኢንቨስትመንት ለመምራትም “የጁንቱ-ኦሞዳ-ጃይኮ” የምርት ማሳያ (ሾውሩም) እና የድህረ ሽያጭ አገልግሎት ማዕከሉን ሰሞኑን ስራ አስጀምሯል።  የጁንቱ ቴክኖሎጂስ ትሬዲንግ የኦሞዳ እና ጃይኮ ቅርንጫፍ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክንዴ መቻል፣ ጁንቱ ቴክኖሎጂስ ከሁለት ወራት በፊት አራት ዓይነት የ“ጂ.ኤ.ሲ” (GAC) የኤሌክትሪክ መኪና ሞዴሎችን ለገበያ ማቅረቡን አስታውሰው፣ በቅርቡ ደግሞ “ኦሞዳ” እና “ጃይኮ” የተሰኙትና…
Read More
በአዲስ አበባ ለ153 ሺህ ውሾች የእብድ ውሻ ክትባት መስጠት ተጀመረ

በአዲስ አበባ ለ153 ሺህ ውሾች የእብድ ውሻ ክትባት መስጠት ተጀመረ

የግብርና ሚኒስቴር እንደገለጸው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ "የእብድ ውሻ በሽታ" እየተባለ የሚጠራውን በንክሻ እና ቡጭሪያ ወደ ሰዎች የሚተላለፍ በሽታን ለማስቀረት ያለመ ክትባት በመሰጠት ላይ መሆኑን አስታውቋል። በሽታው በሰዎች ላይ እስከ ሞት የሚያደርስ አደጋ የሚያስከትል በመሆኑ "የውሻ እብደት"በሽታን ለመከላከል 150 ሺህ ውሾችን ለመከተብ ዕቅድ ይዞ እየሰራ እንደሆነም ሚንስቴሩ አስታውቋል። ከሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የጀመረው ይህ ዘመቻ ለእንስሳቱ የቤት ለቤት ክትባት መስጠትን አላማ ያደረገ እንደሆነ ተገልጿል። ሚኒስቴሩ ከዚህ ቀደም በሀገር አቀፍ ደረጃ ባከናወነው መደበኛ ክትባት ከ100 ሺህ በላይ ውሾችን የከተበ ሲሆን፤ ዘመቻው የውሻ እብደትን ከመከላከል ባለፈ የሰዎችን ደህንነት መጠበቅን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የእንስሳት ጤና መሪ ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ሲሳይ ጌታቸው ተናግረዋል።…
Read More
መንግስት በቀጣዩ ዓመት 1 ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

መንግስት በቀጣዩ ዓመት 1 ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለጸ

የፌደራል መንግሥት በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 8 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡ ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት ያለው ሆኗል። እቅዱ ከዓመታዊ በጀት  ውስጥ የ89  በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ሚንስትሩ አቶ አህመድ ጠቁመዋል። የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ…
Read More
በኢትዮጵያ የሚኖሩ የስሪላንካ ዜጎችን ያገቱ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የሚኖሩ የስሪላንካ ዜጎችን ያገቱ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በኢትዮጵያ የስሪላንካ ኤምባሲ ተወካይ ግንቦት 23/2026 ለስራ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሦስት ዜጎቹ እንደተሰወሩ እና ሲሪላንካ ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ተደውሎ እያንዳንዳቸው 30 ሺ ዶላር እንዲከፍሉ መጠየቃቸውን ግንቦት 26 ቀን 2026  በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ሪፖርት አደረጉ። በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ ወንጀል ፈፃሚዎቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል የክትትልና የምርመራ ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለጸው ከሌሎች የፀጥታ ጉዳይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ በመታገዝ ባሰባሰበው መረጃ ሦስቱ ግለሰቦች በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C- 40463/AA በሆነች ሱዚኪ ዲዛየር  መኪና ከኤርፖርት ተሳፍረው መሄዳቸውን አረጋግጧል። የክትትል ቡድኑ አባላት አሽከርካሪውን  ጨምሮ 2 ኢትዮጵያውያንን እና 4 የፓኪስታን…
Read More
ስምረት ፓርቲ በትግራይ “አዲስ ሕዝባዊ የፖለቲካ ትግል” እንዲጀመር አሳሰበ

ስምረት ፓርቲ በትግራይ “አዲስ ሕዝባዊ የፖለቲካ ትግል” እንዲጀመር አሳሰበ

የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ስምረት (ስምረት)፣ በትግራይ ፖለቲካ ዙሪያ ባወጣው መግለጫ ህወሀት በሀይል ስልጣን መቆጣጠሩን አስታውቋል። በትግራይ ክልል ስልጣን በሀይል የተቆጣጠረው ሀይል ክልሉን ወደ ከፋ የጦርነት ድባብና “ሰው አልባ” መዋቅር እየመራው መሆኑንም አስታውቋል። ፓርቲው የድርጅቱ ምክር ቤት ከግንቦት 29 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄደውን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ማጠናቀቁን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በትግራይ ክልል እየተባባሰ መጥቷል ያለው “የኋላ ቀር ቡድን” ውሳኔ የህልውና አደጋ እየደገነ መሆኑን አስታውቋል። በአሁኑ ወቅት በክልሉ ውስጥ የወጣቶች እፈሳ፣ ከፍተኛ የስደት ፍሰት፣ የምሁራን መበተን እና ከባድ የኑሮ ውድነት መንገሱን ድርጅቱ በዝርዝር አስረድቷል።የስምረት ምክር ቤት በመግለጫው፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ሥልጣን ላይ ያለው “ኋላ ቀር ቡድን የኤርትራን መንግሥት የወታደራዊ…
Read More
ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ከ10 ዓመት በፊት ለተፈጸመ ታክስ ማጭበርበር ቅጣት እንዲጣል የሚፈቅድ ረቂቅ ህግ ተዘጋጀ

ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡ ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡ በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት…
Read More