Eritrea

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ለነበራት ወዳጅነት መበላሸት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተጠያቂ አደረገች

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራት ግንኙነት የተበላሸው በጠቅላይ ሚኒስር አብይ አህመድ አማካኝነት ነው ብላለች፡፡ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት እንደ ቀድሞው አለመሆኑን በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር የሆኑት ዮሃንስ ተክለሚካኤል ተናግረዋል። አምባሳደሩ ይህንን የተናገሩት ባልተለመደ ሁኔታ በብሪታኒያ የኤርትራ ኤምባሲ የዩቲዩብ ቻናል ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ ቪዲዮው ይፋ ከተደረገ ከሰዓታት በኋላ እንዲነሳ መደረጉን ቢቢሲ ዘግቧል። ተሻሽሎ የነበረው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በይፋ የተባለ ነገር ባይኖርም የአገራቱ ግንኙነት ተቀዛቅዟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ እና የስልክ ግንኙነት መቋረጥ ግንኙነቱ ስለመሻከሩ ማሳያ መሆኑ በተደጋጋሚ ሲጠቀስ ቆይቷል። በደቡብ ሱዳን የኤርትራ አምባሳደር ዮሃንስ ተክለሚካኤል ‘ኤርትራ ኤምባሲ ሚዲያ’ (Eritrea…
Read More
ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

በ2010 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ነበር ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለ20 ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን ግንኙነት ያደሱት፡፡ ሁለቱ ሀገራት የመደበኛ የስልክ አገልግሎትን ዳግም ካስጀመሩ ከሰባት ዓመታት በኋላ ተቋርጧል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሐምሌ 2010 ዓ.ም ጀምሮ መደበኛ የስልክ አገልግሎት ሲሰራ የነበረ ሲሆን ከትናንት በስቲያ ማለትም ከመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንደተቋረጠ በኢትዮጵያ ከሚኖሩ ኤርትራዊያን ሰምተናል፡፡ ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ በኢትዮጵያ የሚኖሩ ኤርትራዊ ለአል-ዐይን እንዳሉት “ከማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መደበኛ ስልክ መደወል አልቻልኩም” ብለዋል፡፡ በኤርትራ ኢንተርኔት አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቦቻችንን የምናገኘው በመደበኛ ስልክ ብቻ ነበር የሚሉት እኝህ አስተያየት ሰጩ አገልግሎቱ መቋረጡ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡ “ቀስ በቀስ የኢትዮጵያ እና…
Read More
የኤርትራ ሰራዊት ተጨማሪ ቦታዎችን እየያዘ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ

የኤርትራ ሰራዊት ተጨማሪ ቦታዎችን እየያዘ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ

የኤርትራ ሰራዊት ቀደም ሲል ከያዛቸው አካባቢዎች ውጭ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባብሏል፡፡ የኤርትራ ሰራዊት ከጦርነቱ ወዲህ የያዛቸውን አካባቢዎች በማስፋፋት ከአዲግራት ከተማ በቅርብ ርቀት በ40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል መባሉን ያስተባበሉት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እኔ እስከማውቀው ድረስ የኤርትራ ሰራዊት ከነበረበት አልወጣም አዲስ የያዘውም መሬት ይለም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ሰራዊቱ ቀደም ሲልም ከነበረበት የዛላምበሳ አካባቢ እንዳልወጣ የገለጹት አቶ ጌታቸው እስካሁን ባለኝ መረጃ ወደ አዲግራትም ሆነ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ያደረገው አዲስ እንቅስቃሴ የለም ሲሉ ጥያቄውን አጣጥለዋል፡፡ በኤርትራ ሰራዊት የተያዘው አካባቢ የኢትዮጵያ መሬት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ጉዳዩን የመከታተል ኃላፊነት መሆን የነበረበት የፌዴራሉ መንግስት እንደሆነ በማስታወስም፤ ሆኖም መንግስት በአካባቢው…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መግለጫ ከነገ ነሀሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቆም አስታውቋል፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ እና ከአስመራ ወደ አዲ አበባ የሚደረጉ በረራዎችን አቋርጫለሁ ያለው አየር መንገዱ በኤርትራ ያለው አሰራር አስቸጋሪ እና ከቁጥጥሩ ውጪ መሆኑ ለበረራው መቋረጥ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ ጉዞ ለማድረግ ቲኬት የገዙ መንገደኞችም በመረጡት አየር መንገዶች እንዲበሩ እንደሚያደርግ እና የዋጋ ጭማሪ እንደማያደርግም አየር መንገዱ ገልጿል፡፡ ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ከመስከረም 30 በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር መከልከሏ ይታወሳል፡፡ የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከአንድ ወር በፊት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ በሚጓዙ ተጋዦች ላይ “የተደራጀ እና ስልታዊ የሻንጣ ስርቆት፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ፣…
Read More
ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ “ከመስከረም ወር ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል፡፡ ኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስቴር የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቀጣዩ መስከረም በኋላ ወደ አሥመራ እንዳይበር ማገዱን የሚያሳውቅ ማስታወቂያ በዛሬው እለት አውጥቷል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን አስመለክቱ በሰጠው መግለጫ፤ “የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ሐምሌ 14 2016 ዓ.ም ወይም በፈረንጆቹ 21 ጁላይ 2024 በላከው ደብዳቤ በፈረንጆቹ ከመስከረም 30 ቀን 2024 ዓ.ም. ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ጉዳዩም በበጎ መልኩ እልባት እንደሚያገኝ ያለውን…
Read More
ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የወደብ ስምምነት ዙሪያ የአቋም ለውጥ እንዳላደረገች አስታወቀች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ካነሷቸው ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ፣ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ስለተደረገው የወደብ መግባቢያ ስምምነት እና ሌሎቹም ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ነብዩ እንዳሉት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ጉዳይ በድንበር አካባቢ ያሉ ማህበረሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መንገድ በሁለቱ ሀገራት በሚዋቀር ኮሚቴ ይፈታል ብለዋል። የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ በኤርትራ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለው ድንበር ሊቀየር በማይችል ኹኔታ ለመጨረሻ ጊዜ ተሠምሯል ማለቱ አይዘነጋም። የኤርትራ ጦር በርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን እንደተቆጣጠር እና አካባቢዎቹን ወደ ኤርትራ ማካለሉን እንዴት ኢትዮጵያ እንዴት ታየዋለች? በሚል ለቃል አቀባዩ ለቀረበላቸው ጥያቄም "ጥያቄው…
Read More
አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

አሜሪካ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እንደሚሰጋት ገለጸች

የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት ኮንግረስ የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ የአፍሪካ ጉዳዮች ንኡስ ኮሚቴ፣  ‘”በኢትዮጵያ ተስፋ ወይንስ ስጋት፣ የአሜሪካ ፖሊሲ ሁኔታ’’ ላይ ትላንት ምሸት ምስክርነት ሰምቷል፡፡ የኮሚቴው አባላት ለአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር፣ ስለ ባህር በር በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስለተነሳው ጥያቄ የአሜሪካን አቋም ጠይቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “የወደብ ጉዳይ ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው” ብለው መናገራቸው በቀጠናው ካሉ አገራት አልፎ ለአሜሪካ ስጋት እንደሆነ ማይክ ሐመር ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የባህር በር ፍላጎት በኃይል ተፈጻሚ እንደማይሆን በይፋ እንዲሁም በግል ማረጋገጫ እንደሰጧቸው አመልክተዋል። ጥያቄው በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ስጋት እንደፈጠረ የጠቆሙት ማይክ ሐመር፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ የሚቀጠል ከሆነ…
Read More
የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ስለባህር በር አስተያየት ሲሰጡ እንዲጠነቀቁ ተጠየቀ

ባለስልጣናት ስለ ባህር በር ጉዳይ የሚሰጡት መግለጫ የተጠናና ጥንቃቄ የተሞላበት መሆን እንዳለበት ምሁራን አሳስበዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የባህር በር ዙሪያ የምሁራን ውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ጥናት ያቀረቡና ውይይት ያደረጉ ምሁራን፣ መንግሥት ስለባህር በር የሚሰጣቸው መረጃዎች የጎረቤት አገሮችን የማያሠጉና ጥንቃቄ የተሞላባቸው እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የወደብ አጠቃቀም ለአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና ልማት›› በሚል ርዕስ በተስተናገደው በዚህ ዓውደ ጥናት ላይ፣ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤት መሆን ስለምትችልባቸው አማራጮች ሰፊ ምሁራዊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በጥናት መድረኩ ላይ ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄን በማስመለስ ታሪካዊ ድል ያስመዘገቡ ያለፈው ትውልድ ምርጥ ተሞክሮ ታሪካዊ ድል እንደነበር ተገልጿል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ኤርትራን በፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ ጋር…
Read More
ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስት አብይ አህመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የህዝቧን የመልማት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ የጣላቁ ህዳሴ ግድብን ስትገነባ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ሀገራት ጠይቀዋል፣ እኛም የባህር በር እንዲኖረን መጠየቅ አለብን ሲሉም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል ያበሉ እንጂ ስለየትኛው የባህር በር ግን ስም አልጠቀሱም ነበር፡፡ ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆኑት እና የባህር በር ያላቸው ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማሊያ ሲሆኑ ሶስቱም ሀገራት የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስቀድሞ መግለጫ ያወጣው የኤርትራ መንግስት ሲሆን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣው መግለጫ ሀገሪቱ ሀብቷን ለማንም አሳልፋ እንደማትሰጥ፣ እስካሁንም የተጀመረ ምንም…
Read More
ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኢትዮጵያ በሰኔ ወር መጨረሻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያንን አፈናቀላለች ሲል ገልጿል፡፡ ተመድ ኢትዮጵያ  የኤርትራ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን፤ የስደተኞችን ሕግን በመጣስ እንዲሁም ክስ ሳይኖርባቸው በዘፈቀደ የማሰር እና የማፈናቀል ተግባሯን በአስቸኳይ እንደታቆም ነው ያሳሰበው። ድርጅቱ ወደ ሌላ አገር ጥገኝነት ጠይቀው የገቡ ስደተኞችን በጅምላ ማባረርና በዘፈቀደ ማሰር በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ ነው ሲልም ገልጿል፡፡ በዚህም የመንግሥታቱ ድርጅት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን ጥገኝነት ጠያቂዎችን የማሰቃየት፤ በግዳጅ የማፈናቅልና የሰብአዊ መብት ረገጣ አውግዟል። ኢትዮጵያ በሱዳን ጥገኝነት ጠይቀው ሲኖሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ወደ አገሪቷ የገቡ ኤርትራውያን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ አያያዝ እየተፈጸመች ነው የተባለ ሲሆን፤ ይህም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶችን ሙሉ ለሙሉ የጣሰ ድርጊት…
Read More