bitcoinethiopia

ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ ግብይትን በይፋ ከለከለች

ኢትዮጵያ የክሪፕቶከረንሲ ግብይትን በይፋ ከለከለች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ “የክሪፕቶ አሴትን”  እና የዲጂታል ገንዘብን በኢትዮጵያ መጠቀም የሚያስችል መመሪያ በቀጣይ ሊያወጣ እንደሚችል ገልጿል፡፡ የተቋሙ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ እንደገለጹት ብሔራዊ ባንክ የክሪፕቶ ከረንሲ መመሪያውን የሚያወጣው በማዕከላዊ ባንኪንግ፣ በገንዘብ ፖሊሲ እና በገንዘብ አስተዳደር  ያሉ ዓለም አቀፍ ሁኔታዎችን እያየ መሆኑን ተናግረዋል።  የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ16 ዓመት በፊት የወጣውን እና በስራ ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ አዋጅን አጽድቋል፡፡ በምክር ቤቱ ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት አቶ ማሞ አዲሱ አዋጅ ካካተታቸው አዳዲስ ድንጋጌዎች መካከል ክሪፕቶ ከረንሲ እና የዲጂታል ገንዘብን መጠቀም የተመለከቱት ይገኙበታል፡፡ የጸደቀው አዋጅ “አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ብሔራዊ ባንክ ካልፈቀደ በስተቀር፤ ክሪፕቶ ከረንሲ ወይም ሌላ ማንኛውንም ዲጂታል…
Read More
ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት ዳታ ማይኒንግ ኩባያዎች 27 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከውጭ ሀገራት ዳታ ማይኒንግ ኩባያዎች 27 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ለጎረቤት አገራት ከሸጠው ኤሌክትሪክ ኃይል ከ31 ሚሊዮን ዶላር በላይ ማግኘቱን አስታወቀ። ተቋሙ ለጅቡቲ ከሸጠው ከ169 ሺሕ 710 ሜጋ ዋት በላይ የሚኾን ኃይል፣ 10 ሚሊዮን 379 ዶላር እና ለኬንያ ከሸጠው ከ314 ሺሕ 931 ሜጋ ዋት በላይ የሚኾን ኃይል ከ20 ሚሊዮን 470 ሺሕ ዶላር ማግኘቱ ተገልጿል። በተመሳሳይ፣ ተቋሙ ለሱዳን ካቀረበው ከ13 ሺሕ 185 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ከ659 ሺሕ በላይ ዶላር ያገኘ ሲኾን፣ በሱዳኑ ጦርነት ሳቢያ ተቋሙ በሩብ ዓመቱ ለአገሪቱ ለማቅረብ ካቀደው ኃይል ውስጥ ያቀረበው 15 በመቶውን ብቻ እንደኾነ ተገልጧል። ኢትዮጵያ ውስጥ በዲጂታል መረጃ ማቀነባበር ከተሠማሩ የውጭ ኩባንያዎች በሩብ ዓመቱ ውስጥ ከተሸጠው ኤሌክትሪክ ኃይል ደግሞ፣…
Read More
የአሜሪካው ቢትኮይን ክሪፕቶከረንሲ ኩባንያ በኢትዮጵያ መሰማራቱን ገለጸ

የአሜሪካው ቢትኮይን ክሪፕቶከረንሲ ኩባንያ በኢትዮጵያ መሰማራቱን ገለጸ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የምናባዊ ገንዘብ ወይም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት ፍላጎት እየጨመረ ሲሆን በኢትዮጵያም አጀንዳ ከሆነ አምስት ዓመት ሆኖታል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የትኛውንም ክሪፕቶ ከረንሲ ግብይት እንዳልፈቀደ እና ግብይት ሲፈጽሙ የተገኙ ሰዎችም በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስታውቆ ነበር፡፡ ካሳለፍነው ዓመት ጀምሮ በኢትዮጵያ የቢትኮይን ግብይት መፈጸም የሚያስችሉ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያደርጉ ኩባያዎች ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል፡፡ ኢትዮጵያ አሁንም የክሪፕቶከረንሲ ግብይት እንዲደረግ ያልፈቀደች ሲሆን የዳታ ማዕከል ግንባታዎች እንዲካሄዱ ግን ስምምነቶችን በመፈራረም ላይ ነች፡፡ መቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው የዎልስትሪቱ ቢትፉፉ የተሰኘው የክሪፕቶከረንሲ ኩባንያ በኢትዮጵያ መሰማራት የሚያስችለውን ሂደት መጀመሩን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው የክሪፕቶከረንሲ ግብይት ማካሄድ የሚያስችል የ80 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ሀይል መሰረት ልማት መግዛቱን ገልጿል፡፡ ቢትፉፉ የተሰኘው ይህ…
Read More