13
Nov
በክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች ጭምር በመታገዝ ህገ ወጥ የምንዛሬ ዝውውር ያደርጉ ነበር የተባሉ ቻይናውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ በተቀናጀ መንገድ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ደረስኩባቸው ያላቸውን 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ያስታወቀው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት 8 ቻይናውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ለመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች በላከው መግለጫ ይፋ አድርጓል። በመግለጫው በተደራጀ መንገድ በስውር ሲፈጸም ነበር ያለውን ህገ ወጥ የምንዛሬ ገንዘብ ዝውውርና አሻጥር ለማምከን የሚያስችል ምስጢራዊ የመረጃ ስምሪቶችን ሲያደርግ እንደቆየ ያስታወቀው አገልግሎቱ ቻይናውያኑን ጨምሮ 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፤ ከሕገ - ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው አምስት መቶ አስራ ዘጠኝ የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን እንዲሁም የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውን…