New admin

953 Posts
ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ኢትዮጵያ የምርጫና ፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ህጓን አሻሻለች

ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን በስድስት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድደዉ አዋጅ ፀድቋል። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ጉባኤ የምርጫ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል። አዋጁ ከነባሩ አዋጁ 1162/2011ዉስጥ የነበሩ 26 አንቀጾችን ያሻሻለ ሆኖ የቀረበ ነዉ ተብሏል። አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ለመወዳደር ከ 6 ክልሎች የ60 በመቶ ድጋፍ ፊርማ ማሰባሰብን የሚያስገድድ አንቀፅ ይገኝበታል። ከዚህ ቀደም ሀገራዊ ፓርቲ ለመሆን የአራት ክልሎች የድጋፍ ፊርማ የሚያስፈልግ ሲሆን ይህንን አንቀፅ ለማሻሻል ያስፈለገበት ምክንያት የተጨመሩ ክልሎች መኖራቸዉን ታሳቢ አድርጎ መሆኑን ምክር ቤቱ ገልጿል። በዚህ መሰረት ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት በስድስት ክልሎች የድርጅት አባል ማፍራት እንዳለባቸዉ የሚያደርግ ነዉ። አንድ የምክር ቤት አባል የሀገራዊ ፓርቲ ምስረታን…
Read More
በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት መሰጠቱ ተገለጸ

የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2017 በጀት ዓመት ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች ፓስፖርት መስጠቱን አስታውቋል። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት እንዳሉት ለፓስፖርት አመልካቾች የተቀላጠፈ አገልግሎት በመሰጠቱ ምክንያት የአመልካቾች ቁጥር ቀንሷል ብለዋል። ተቋሙ የኢ-ፓስፖርት ለመስጠት ያስቀመጠውን እቅድ በአዲስ አበባ ጎተራ ባለው ቅርንጫፍ ማስጀመሩም ተገልጿል። ይሁንና ተቋሙ ፓስፖርት ቤት ለቤት መስጠት እጀምራለሁ በሚል የያዘው እቅድ እስካሁን ስለመጀመሩ ዳይሬክተሯ አልገለጹም። ይህ በዚህ እንዳለም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ3800 በላይ ሰዎች በተጭበረበረ ሰነድ ፓስፖርት ለማውጣት ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል ተብሏል። ተቋሙ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ፓስፖርት ለማግኘት የሚሞክሩ ሰዎችን የመቆጣጠሩ አቅሙ ያደገው ተቋማዊ ደህንነትን የማረጋጫ ሥርዓት ዘርግቷልም ተብሏል።  ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከሰራተኞች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን በማጉላላት እና…
Read More
መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

መንግስት ከግምጃ ሰነድ ግዢዎች 173 ቢሊዮን ብር እንደሚሰበስብ ገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን፣ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ማዕከላዊ ግምጃ ቤት ሰነዶች ሽያጭን በይፋ አስጀምረዋል። የገንዘብ ሚንስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ጊዜ እንዳሉት መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ማቅረቡን ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ውስጥ መንግስት ከበጀተው 1.9 ትርሊዮን ብር ውስጥ 188 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት እንዳለበት ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ከገጠመው የበጀት ጉድለት ውስጥም 173 ቢሊዮን ብሩን ግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ በማቅረብ ለመሰብሰብ መታቀዱንም አቶ አህመድ ተናግረዋል፡፡ የሀገር ውስጥ ብድሩ ከሰነድ ገዢዎች የሚሰበሰበው የዋጋ ግሽበትን በማያባብስና የማክሮ ኢኮኖሚውን በማያናጋ መልኩ እንደሚሆንም ገልጸው ነባር የግምጃ ሰነዶችን ወደ ኤሌክትሮኒክስ መንገድ ስራዎች እየተቀየሩ መሆኑን፣ አዳዲስ ግምጃ ሰነዶችም በዚህ መልኩ ለገበያ ይቀርባሉም…
Read More
ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

ቻይና የኢትዮጵያን አኩሪ አተር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

የቻይና ጉምሩክ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ቻይና ከአሜሪካ ጋር እየተካረረ የመጣውን የንግድ ውጥረት ተከትሎ የፕሮቲን አቅርቦቶቿን ለማስፋት ባላት ፍላጎት ከኢትዮጵያ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶችን እንዲገቡ ፈቃድ መስጠቷን ኒውስ ሴንትራል ዘግቧል። የኢትዮጵያ አኩሪ አተር ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ ቻይና እንዲገቡ ተፈቅደዋል። ቻይና ለአገር ውስጥ የአኩሪ አተር ምርት በአብዛኛው በአኩሪ አተር ምርቶች ከብራዚል እና ከአሜሪካ ታስመጣለች። ቻይና በሰኔ ወር ከኡራጓይ የሚገቡ የአኩሪ አተር ምርቶች እንዲገቡ ፈቅዳለች፤ ኢትዮጵያ ደግሞ አሁን  ሩሲያ፣ ቤላሩስ፣ አርጀንቲና እና ብራዚልን ጨምሮ እውቅና የተሰጣቸውን የአቅራቢዎች ዝርዝርን  ተቀላቅላለች። ቻይና የኢትዮጵያ ቁጥር አንድ የንግድና ኢንቨስትመንት አጋር ስትሆን ዓመታዊ የንግድ ልውውጥ መጠን ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ ደርሷል። ኢትዮጵያ በተለይም ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ የጣለውን አስገዳጅ የቦንድ ግዥ አነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ መወሰኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው። "አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል። ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ እቅዷን ሰረዘች

መንግስት  ከኦጋዴን ተፋሰስ የተፈጥሮ ጋዝ በጅቡቲ በኩል በቧንቧ መስመር ወደ ውጭ የመላክ እቅዱን የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መጓተትን በመጥቀስ በይፋ ሰርዟል። በኢትዮጵያ ኢነርጂ አውትሉክ 2025 የተረጋገጠው ይህ ስረዛ፣ በሀገራዊ የኢነርጂ ፖሊሲ ውስጥ ትልቅ ለውጥ የሚያሳይ ሲሆን፣ ከውጭ የመላክ ፍላጎት ወደ ሀገር ውስጥ አጠቃቀም እየተሸጋገረ መሆኑን ያመለክታል ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። “የኢትዮጵያ መንግስት በኦጋዴን ክልል የታቀደውን የተፈጥሮ ጋዝ ማውጣት እና የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ወደ ጅቡቲ የሚዘረጋውን የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት ሰርዟል” ሲል ሪፖርቱ ይገልጻል። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በጋራ የተዘጋጀው የኢነርጂ አውትሉክ “የፕሮጀክት ፋይናንስን በማግኘት ረገድ ያሉ ችግሮች እና የፕሮጀክት ትግበራ…
Read More
በአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦሸማኔዎች ከኢትዮጵያ የተሰረቁ ናቸው ተባለ

በአረብ ሀገራት የሚገኙት አቦሸማኔዎች ከኢትዮጵያ የተሰረቁ ናቸው ተባለ

በኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ሀብት ላይ ከተደቀኑ በርካታ ችግሮች መካከል ህገወጥ የእንስሳት ዝውውር አንዱ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል። በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት ህገወጥ ዝውውር ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዳንኤል ጳውሎስ  እንደተናገሩት ለተለያዩ አላማዎች ሲባል በኢትዮጵያ የሚገኙ የዱር እንስሳት ከነህይወታቸው በህገወጥ መንገድ ይዘዋወራሉ። በዚህ መልኩ ከሀገር የሚወጡ እንስሳቶች በርካታ ቢሆኑም  በቀዳሚነት አቦሸማኔ ይጠቀሳል ። አቦሸማኔ በተለይም በምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል በሱማሌ ክልል መኖሪያውን በማድረጉ የአካባቢው ማህበረሰቦች ባካበቱት ተፈጥሮአዊ ዘዴ የአቦ ሸማኔ ቡችላዎችን በመያዝ ሶማሌላንድ አካባቢ ለሽያጭ እንደሚያቀርቡ ተጠቁሟል። በዚህ መልኩ ይህ እንስሳ ወደ መካከለኛው የአረብ ሀገራት ጭምር ላሉ ባለሀብቶች የሚሸጥበት ሁኔታ መኖሩን የገለፁት አቶ ዳንኤል ግለሰቦቹ የራሳቸው የሆነ መካነ አራዊት…
Read More
ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ሀገራቸው አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስተያየት ውድቅ አድርጓል። የጽህፈት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ ፕሬዝዳንቱ ቱርዝ ሶሻል ተብሎ በሚጠራው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዩናይትድ ስቴትስ የህዳሴ ግድብን በገንዘብ ደግፋለች ማለታቸውን "መሠረተ ቢስ" ብለውታል። ኃላፊው "ህዳሴ ግድብ ከ20ዐ3 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት፣ ጉልበት፣ እውቀትና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለ ነው” ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል። አክለውም የአሜሪካው መሪ ንግግር ከዓለም አቀፋ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተናግረዋል። ከ15 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ…
Read More
በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች እንዲሰሩ ተፈቀደ

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል። መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል። ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል። ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል። ብሔራዊ…
Read More
የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የመንግስት ተቋማት ስራ ለለቀቁና ለሞቱ ሰራተኞች ከ400 ሺህ በላይ ብር ደመወዝ ከፍለዋል ተባለ

የፌደራል ዋና ኦዲተር የመንግስት ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት የበጀት ኦዲት አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ዋና ኦዲተር በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 17 የመንግስት ተቋማት በጡረታ፣ በሞትና በሌሎች ምክንያት ከሥራ ለለቀቁ ሰራተኞች 408,462 ብር ያላግባብ ደመወዝ ከፍለው ተገኝተዋል ተብሏል፡፡ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ሁኔታ ካልተፈቀደ  በስተቀር የሰራተኞች ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገትና ዝውውር እንዳይፈጸም ቢከለክልም በስምንት መስሪያ ቤቶችና በአንድ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በጠቅላላው 24,073,003 ብር የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ በቋሚ የሥራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን በኮንትራት በመቅጠር ክፍያ ፈጽመዋልም ተብሏል፡፡ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሳያስፈቅዱ የኮንትራት ቅጥር ከፈጸሙት ተቋማት መካከል የቅደስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ ሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ፣…
Read More