11
May
ከአምስት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ላለፉት ዓመታት ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ማድረጉን ገልጿል። ለኢንቨስትመንት ያወጣውን ወጪ ሳይመልስ የቆየው ኩባንያው ኪሳራው እየቀነሰ መምጣቱን ገልጾ በቀጣዮቹ ወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትርፍ እንደሚገባ አስታውቋል። መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን ይህም ከቀዳሚው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር የ130 በመቶ ብለጫ አንዳለው የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄሌፑት ገልጸዋል፡፡ በጊዜው ኩባንያው 39.5 ቢሊዮን የኬንያ ሽልንግ ወይም 47.7 ቢሊዮን ብር አካከባቢ ኪሳራ አስመዝግቧል፡፡ ኪሳራው አምና በተመሳሳይ ጊዜ ከተመዘገበው በግማሽ ያህል መቀነሱንም ዋና ስራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል፡፡ ኩባንያው በዓመቱ ውስጥ ካገኘው 15.9 ቢሊዮን ብር ውስጥ 9.6…