ኢኮኖሚ

ሄኒከን ቢራ ፋብሪካ ከግል ድርጅቶች ቁጥር አንድ ግብር ከፋይ ኩባንያ ተባለ

ሄኒከን ቢራ ፋብሪካ ከግል ድርጅቶች ቁጥር አንድ ግብር ከፋይ ኩባንያ ተባለ

ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብር ከግብር የሰበሰበች ሲሆን ከግል ድርጅቶች ሄኒከን ቢራ ቁጥር አንድ ግብር ከፋይ ተቋም ሆኗል። ከአራት በላይ የቢራ ብራንዶችን ለኢትዮጵያ ገበያ በማምረት ላይ ያለው የጀርመኑ ሄኒከን ኩባንያ 26 ቢሊዮን ብር እንደከፈለ ተገልጿል። ሄኒከን እንደሀገር ከፍተኛ ግብር ከሚከፍሉ ተቋማት መካከል በአራተ ደረጃ ላይ ስሙ ተጠቅሷል። በዚህ በጀት ዓመት ለመንግስት 10 ከፍተኛ ግብር ከፋይ ድርጅቶች መካከል 7ቱ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ናቸው።ኢትዮ ቴሌኮም 66  ቢሊዮን ብር  በመክፈል እንደ ሀገር ቁጥር አንድ ግብር ከፋይ ተቋም ነው። ሁለተኛው ግብር ከፋይ ተቋም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሆን ከፈለው 37 ቢሊዮን ብር ሲከፍል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደግሞ 31 ቢሊዮን ብር እንደከፈለ…
Read More
ሰባት የክሪፕቶከረንሲ ድርጅቶች መተግበሪያ በኢትዮጵያ እንዳይሰሩ ታገዱ

ሰባት የክሪፕቶከረንሲ ድርጅቶች መተግበሪያ በኢትዮጵያ እንዳይሰሩ ታገዱ

መንግሥት፣ ለሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ሽፋን ይሠጡ የነበሩ ሰባት የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ማገዱን አስታውቋል። ለሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ ነበሩ የተባሉ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች ሙሉ በሙሉ መታገዳቸውን የመንግስት ኮሙንኬሽን ሚንስትር እናታለም መለሰ ተናግረዋል። ስማቸው ያልተጠቀሱት እና የታገዱት እነዚህን መተግበሪያዎች በመጠቅም ዜጎች ገንዘባቸውን እንዲበሉ፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲደረግ ሲያደርጉ እንደነበር ተገልጿል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የትኛውም የምናባዊ መገበያያ መንገዶች መከክልከላቸውን በተደጋጋሚ ሲናገር ቆይቷል። ከዚህ በተጨማሪም መሰረታቸውን በኢትዮጵያ ላደረጉ 36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ አራት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ አመራሮች መታሰራቸውም ተገልጿል። እንዲሁም ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ…
Read More
በኢትዮጵያ ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሙስናን አስመልክቶ ያለውን ግንዛቤ የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ፣ የመሬትና የገቢዎች ተቋማትን ጨምሮ በበርካታ ተቋማት ውስጥ ሙስና አሳሳቢ መሆኑን ማረጋገጡን አስታውቋል። የመሬት አስተዳደርና የይዞታ ምዝገባ፣ የገቢዎችና ታክስ ጽሕፈት ቤቶች፣ የኮንስትራክሽን ፈቃድ ቁጥጥር፣ የንግድና ትራንስፖርት ቢሮዎች፣ የወረዳና የቀበሌ አስተዳደሮች በከፍተኛ ደረጃ ለሙስና ተጋላጭ መሆናቸው በጥናቱ ተለይቷል ብሏል፡፡ ኮሚሽኑ ለዳሰሳ ጥናት በተወሰደ ናሙና ከ60 በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ሙስና በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ተግባራት ከፍተኛ እንቅፋትና ችግር የፈጠረ አሳሳቢ ችግር መሆኑን እንደነገሩት ገልጿል፡፡ በአቋራጭ የመበልፀግ ፍላጎት፣ የሥነ ምግባር ጉድለት፣ ውስብስብና ግልጽ ያልሆኑ የአገልግሎት አሰጣጥ ሒደቶችና የሕግ ማስከበር ድክመቶች ለሙስና መስፋፋት ዋነኛውንና ቀዳሚውን ድርሻ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ የጥናት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ በጥናቱ…
Read More
ከደላሎች ውጪ ሰራተኞችን ከቀጣሪዎች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ መተግበሪያ ተዘጋጀ

ከደላሎች ውጪ ሰራተኞችን ከቀጣሪዎች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ መተግበሪያ ተዘጋጀ

የቤት ውስጥ ሰራተኛን ጨምሮ የግል አገልግሎት ሰራተኞች እና አሰሪዎችን የሚያገናኝ፣ ደላላን የሚተካ መተግበሪያ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። የግል አገልግሎት ቅጥር የሚባሉትን እንደ አትክልተኛ፣ የቤት ውስጥ ተንከባካቢ፣ የቤት ውስጥ አብሳይ (ሼፍ) እና ሌሎችም ዘርፎች የቅጥር ግንኙነት ከደላላ ጣልቃ-ገብነት የሚያላቅቅ መተግበሪያ እና አዲስ ደንብ እየተዘጋጀ እንደሆነ ተገለጸ። ዓለም አቀፍ የሥራ ድርጅት ኮንቬንሽን 189ን ታሳቢ አድርጎ የተዘጋጀው ደንብ ለፍትሕ ሚኒስቴር መቅረቡን እና በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል። አንድ ዓመት አካባቢ ለሚፈጅ ጊዜ ግብዓት በማሰባሰብ እና ባለድርሻ አካላትን በማወያየት የተዘጋጀው ደንብ፣ የቤት ሠራተኞች መመዝገቢያ ሶፍትዌር ሲስተም እንዲኖረው የሚያስችል መተግበሪያ እየተዘጋጀለት እንደሆነ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ…
Read More
የባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ከ157 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

የባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ከ157 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

በመካከለኛው ምስራቅ እና በቀይ ባህር ዙሪያ ያለው ጦርነትና ውጥረት ለስራው ፈተና እንደነበር፣ የነዳጅ እጥረትም እንደልብ ለመንቀሳቀስ መቸገርን ጨምሮ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት ፈተና እንደነበሩ አስረድቷል። የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ በተመለከተ ዛሬ ከሰዓት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው ዓመቱ ለዘርፉ ፈታኝና ከባድ ጊዜ ቢሆንም በብዙ መለኪያዎች ግን የተሻለ ሊባል የሚችል ስራ የተሰራበት እንደነበር ጠቁመዋል። በበጀት ዓመቱ ተቋሙ በአጠቃላይ ከ7 ሚሊዮን በላይ ሜትሪክ ቶን ጭነት ማጓጓዝ መቻሉን የተናገሩት ሀላፊው ከዚህ ውስጥ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶኑ ከኮንቴይነር ውጪ የሆነ ጭነት፣ 2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶኑ ደግሞ የኮንቴይነር ጭነት እንደሆነ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ9 ቢሊዮን በላይ ዶላር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ9 ቢሊዮን በላይ ዶላር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ2025/2026 በጀት ዓመት የዓለም አቀፍ ፈተናዎችንና የነዳጅ ዋጋ ጭማሪን በመቋቋም 9.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ገልጿል። አየር መንገዱ በዓመቱ 20.7 ሚሊዮን ደንበኞችን በማጓጓዝ የ10 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን፣ የጭነት አቪየሽን አገልግሎቱም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ​የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ፣ በበጀት ዓመቱ አራት አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር አጠቃላይ የመዳረሻዎችን ቁጥር 150 ማድረሱን ገልጸዋል። በተጨማሪም የሀገር ውስጥ መዳረሻዎችን ከ22 ወደ 25 ከፍ በማድረግ የአየር መንገዱን ተደራሽነት ማስፋፋት ተችሏልም ብለዋል። የበረራ አቅምን ለማጠናከርም ዘጠኝ አዳዲስ አውሮፕላኖች በግዢና በኪራይ ወደ ሥራ የገቡ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያ አቪየሽን ዩኒቨርሲቲ ስልጠና የሚውሉ ስምንት…
Read More
ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን የብድር ገደብሙሉ በሙሉአነሳ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው 7ኛ ስብሰባው፣ የተለያዩ የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦችን አቅርቦ ማጽደቁን አስታውቋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠርና ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ያለመ አዳዲስና ወሳኝ የፖሊሲ ውሳኔዎችን ማሳለፉን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቋል። ኮሚቴው ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ በሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መወሰኑንም ገልጿል። እስካሁን ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ ተጥሎ የነበረው የ24 በመቶ ቀጥተኛ የብድር ዕድገት ገደብ ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል። በባንኮች ላይ የብድር ገደብ ውሳኔ ተጥሎ የነበረው ኢኮኖሚው በወለድ ምጣኔ ላይ ወደተመሠረተ የገንዘብ ፖሊሲ ሥርዓት እስኪሸጋገር እንደነበር…
Read More
የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ላኪዎች የዩኬን የቀረጥ ነፃ ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀረበ

የኢትዮጵያ ነጋዴዎችና ላኪዎች የዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ታዳጊ ሀገራትን ተጠቃሚ የሚያደርገውን የንግድ ሥርዓት በተሻለ ሁኔታ ተጠቅመው ወደ ዩኬ ገበያ የመግባት ዕድላቸውን እንዲያሰፉ ጥሪ ቀረበ። ይህ ጥሪ በአዲስ አበባ በተካሄደው የሥልጠና መድረክ ላይ የተላለፈ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ላኪዎች የዕድሉን፣ የመስፈርቶቹንና የተግባራዊ ሂደቶቹን ግንዛቤ እንዲያሳድጉ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል። በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፣ ከዩኬ የንግድና ልማት መሥሪያ ቤት፣ ከብሪታንያ ኤምባሲና ከኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ የዩኬ ገበያ ለመግባት የሚያስፈልጉ የጥራት ደረጃዎችና የቁጥጥር መስፈርቶች ተብራርተዋል። አምባሳደር ብሩክ መኮንን እንደገለጹት፣ ቡና፣ የግብርና ምርቶችና ጨርቃጨርቅ በዚህ ሥርዓት ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ የወጪ ንግድ ዘርፎች ናቸው። ሆኖም፣ የቀረጥ ቅናሹ ብቻውን…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ የብድር ስምምነት ዙሪያ እንድትጠነቀቅ የዓለም ባንክ አሳሰበ

ኢትዮጵያ በአዲስ የብድር ስምምነት ዙሪያ እንድትጠነቀቅ የዓለም ባንክ አሳሰበ

ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር ያፀደቀው የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ከአዳዲስ የብድር ጫና እንድትቆጠብ አስጠንቅቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከእዳ ጫና እንድትላቀቅ በምትፈጽማቸው አዳዲስ የብድር ስምምነቶች ዙሪያ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ልትወስድ እንደሚገባ አስታውቋል። ተቋሙ አምስተኛውን የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ግምገማ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ተጨማሪ 464 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለኢትዮጵያ አጽድቋል። የተቋሙ የበጀት ድጋፍ ከሁለት አመት በፊት ያፀደቀውና ለአራት አመት በሂደት የሚለቀቅ በሚል የፈቀደው የ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ብድር አካል ነው፡፡ የአይኤምኤፍ የስራ አመራር ቦርድ ያፀደቀው የ464 ሚሊዮን ዶላር ብድር እስካሁን በአራት ዙር ከተለቀቀው ሁሉ የላቀ ሲሆን ለወደፊቱ ከሚለቀቀው ብድር ታሳቢ የሚደረግ የ200 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ ታክሎበታል። ጭማሪ ገንዘቡ…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ

መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተያዘው በጀት ዓመት 80 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል። የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለጹት፣ የተገኘው ትርፍ ባንኩ ባለፉት ጊዜያት ካጋጥሙት የህልውና አደጋ መውጣቱን ያሳያል ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም ባንኩ ከስድስት ዓመታት በፊት ከነበረበት ችግር ወጥቶ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ደረጃ ቀዳሚ ከሚባሉ ጠንካራ ባንኮች ተርታ መሰለፉንም ተናግረዋል። ባንኩ ለደረሰበት ከፍተኛ የትርፍ መጠን በዋናነት ለግል ዘርፉ የሰጠው ትኩረት፣ የተበላሸ ብድር መጠን መቀነሱ እና የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት መስፋፋትን በምክንያትነት አንስተዋል። ባንኩ እየተጠናቀቀ ባለው የዘንድሮው በጀት ዓመት 648 ቢሊዮን ብር አዲስ ብድር እንደሰጠም ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል። ከተሰጠው ብድር ውስጥም 90 በመቶ የሚሆነውን ወይም 588 ቢሊዮን ብር ለግል ዘርፍ መቅረቡም ተገልጿል።…
Read More