21
Mar
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ። ሲቢኢ ካፒታል አክሲዮን ኢንቨስትመንት ባንክ እና ወጋገን ካፒታል አክሲዮን ማህበር ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ያገኙት የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንኮች ሆነዋል። እነዚህ ባንኮች ራሳቸውን ችለው የተቋቋሙ የካፒታል ገበያ ስራ ብቻ የሚሰሩ የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው የተባለ ሲሆን በተጨማሪም ለአምስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፈቃድ ተሰጥቷል። ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች መካከልም ኢትዮ-ፊደሊቲ ሴኩሪቲስ አ.ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ (Securities Dealer) ፣ ኤች ኤስ ቲ ኢንቨስትመንት አድቫይዘሪ ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ፣ ኢኩዥን የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ መሆናቸው ተጠቁሟል። ፈቃድ የተሰጣቸው አገልግሎት ሰጪዎች…