CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ወጋገን ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ። ሲቢኢ ካፒታል አክሲዮን ኢንቨስትመንት ባንክ እና ወጋገን ካፒታል አክሲዮን ማህበር ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ያገኙት የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንኮች ሆነዋል። እነዚህ ባንኮች ራሳቸውን ችለው የተቋቋሙ የካፒታል ገበያ ስራ ብቻ የሚሰሩ የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው የተባለ ሲሆን በተጨማሪም ለአምስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፈቃድ ተሰጥቷል። ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች መካከልም ኢትዮ-ፊደሊቲ ሴኩሪቲስ አ.ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ገበያ አከናዋኝ (Securities Dealer) ፣ ኤች ኤስ ቲ ኢንቨስትመንት አድቫይዘሪ ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ፣ ኢኩዥን የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ ኃ.የተ.የግ. ማ - የሰነድ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪ መሆናቸው ተጠቁሟል። ፈቃድ የተሰጣቸው አገልግሎት ሰጪዎች…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ወለድ መጠኖች ላይ ጭማሪ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከየካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ በተለያዩ የብድር ዓይነቶች ላይ ጭማሪ ማድረጉን አስታዉቋል። ይህ ጭማሪ የመጣው መንግስት የፋይናንስ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ እያደረገ ያለው ጥረት አካል እንደሆነ ባንኩ ገልጿል። በተደረገው ማስተካከያ መሰረት፣ የግብርና ብድሮች እስከ 15.5%፣ የንግድ ብድሮች እስከ 18%፣ የወጪ ንግድ ብድሮች እስከ 14%፣ የግል ብድሮች ደግሞ እስከ 15% ጭማሪ አሳይተዋል። ይሁንና ባንኩ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ወይም ኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድሮች የወለድ ምጣኔው በነበረበት በ12 በመቶ እንደሚቀጥል አስታውቋል። የውጭ ምንዛሬ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰራተኞች የግል ብድሮች በስምምነቱ ውል ላይ በመመስረት ከ11 በመቶ እስከ 13 በመቶ የሚደርስ ሲሆን፣ ለየት ያለ ከፍተኛ ዋጋ ላላቸው ደንበኞች ሰራተኞች የግል ብድሮች…
Read More
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብድር መስጠት አቆመ

በኢትዮጵያ ካሉ የንግድ ባንኮች መካከል አንጋፋ እና ሀብታም የሆነው የንግድ ባንክ ብድር መስጠቱን አቁሟል፡፡ ንግድ ባንኩ ብድር ለማግኘት የተለያዩ ሂደቶችን አልፈው ፤ ብድሩ ተፈቅዶላቸው የመልቀቅ ሂደት ላይ ያሉትም እንዲቆም ማዘዙ ተገልጿል፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የባንኩ ደንበኛ ለኢትዮ ነጋሪ እንዳሉት የንግድ ባንክ ብድር ተፈቅዶልኝ ገንዘቡን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ እያለሁ ብድሩ ለጊዜው እንዲቆም መወሰኑ ተነግሮኛል ብለዋል፡፡ ሌላኛው የባንኩ ደንበኛ በበኩሉ ሶስት ሚሊዮን ብር ብድር ለመውሰድ አስፈላጊውን መስፈርቶች ሁሉ አሟልቼ ብሩ እንዲለቀቅልኝ እየተጠባበቅሁ እያለ የቅርንጫፉ ስራ አስኪጅ ደውለው ብድሩ መታገዱን ነገሩኝ ሲልም ነግሮናል፡፡   ባንኩ ብድር እንዲቆም ትእዛዝ ያስተላለፈው ከመጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ነውም ተብሏል፡፡ ንግድ ባንኩ በጊዜያዊነት ብድር መልቀቅ…
Read More
ንግድ ባንክ ከተወሰደበት ጠቅላላ ገንዘብ ውስጥ 372 ሚሊዮን ብር ማስመለሱን አስታወቀ

ንግድ ባንክ ከተወሰደበት ጠቅላላ ገንዘብ ውስጥ 372 ሚሊዮን ብር ማስመለሱን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሁለት ሳምንት በፊት ያጋጠመውን የሲስተም ችግር አስመልክቶ እያደረገ ያለውን ስራ የደረሰበት ደረጃ ላይ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በሰጡት መግለጫ፤ ችግሩ የት ጋር ነው ያጠመው የሚለው ላይ በባለሙያ ጥናት እየተደረገ ነው ገና አላለቀም ብለዋል። በእለቱ ከተፈጠረው የሲስተም ችግር ጋር ተያይዞ በተደረጉ ግብይች እና የገንዘብ ዝውወሮች ዙሪያም ማብራሪያ ሰጥተዋል። በእለቱ ሊጠፋ የነበረ ወይም አንድ ሰው ገንዘብ ከአካውንቱ ገንዘብ ካስተላለፈ በኋላ ለተላከለትም ሰው ደርሶ ገንዘቡ ለላኪውም ተመለሶ የተተካ ወይም ሪቨርስ ያደረገ 801 ሚሊየን 417 ሺህ 800 ብር  ነበር ብለዋል። በእለቱ አጋጥሞ በነበረ የሲስተም ችግር በነበረበት መስመር ላይ 25 ሺህ 761 ደንበኞች ገብይት ፈጽመዋል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤…
Read More
በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

ንግድ ባንክ ባሳለፍነዉ አርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ባጋጠመዉ ችግር 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉና 2.6 ቢሊየን ብር መንቀሳቀሱን አስታውቋል ባንኩ ገንዘብ የወሰዱ ሰዎችን ለመጠየቅና ገንዘቡን ለማስመለስ ግብረሀይል ያቋቋመ ሲሆን በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ገምተዋል፡፡ ቅዳሜ ዕለት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙ ተገልጿል፡፡ ግብረ ሀይሉ ከብሔራዊ ባንክና ከንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት የተካተቱበት ነው የተባለ ሲሆን ዓላማው ደግሞ በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ማስመለስ እና ማጣራት ነው፡፡ ይሁንና ባንኩ በተባለው ሰዓታት ውስጥ የተወሰደበትን የገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ፡፡ ከሁለት ጨዋታዎች በፊት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሀ የከፍተኛ ሊግ ውድድር የመዝጊያ ስነ-ሥርዓት ላይ ዋንጫውን አንስቷል፡፡ ቡድኑ ቀሪ የመርሐ ግብር ጨዋታውን ከቀኑ 6፡00 ላይ ከሰንዳፋ በኬ ጋር በማድረግ 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎ ነጥቡን 60 ማድረስ ችሏል፡፡ በውድድሩ የመዝጊያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመርቻንት እና ኤጀንት ባንኪንግ ዳይሬክተር አቶ ብሌን ኃ/ሚካኤል እና ሌሎች እንግዶች ለሻምፒዮኑ ቡድን እና ለሌሎች ተሸላሚዎች…
Read More
የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ትልቁ ባንክ ከቻይናው የቴክስታይል ኩባንያ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ ከሚያቀርብ የቻይና ቴክስታይል ኩባንያ ጋር ተፈራርሟል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሠራተኞቹ የደንብ ልብስ አቅርቦት ከቻይናው ጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ጋር መፈራረሙን አስታውቋል። የንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ ጥራት ያለው የደንብ ልብስ ለሠራተኞች እንዲቀርብ የሚያስችል ውይይት ከጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ ተወካዮች ጋር መወያየታቸው ተመላክቷል፡፡ ለደንብ ልብስ አቅርቦቱ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ በመመደብ ለአብዛኛው ሠራተኛ ወጪውን የሸፈነ ሲሆን፣ በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ የባንኩ ሠራተኞች እንዲሁም የሥራ ኃላፊዎች ደግሞ የተወሰነ ወጪ ተጋርተው የሚቀርብ መሆኑን አቶ አቤ ገልፀዋል፡፡ የጂያንግሱ ሰንሻይን ግሩፕ በኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚ/ር ጋዊ ቻንሁሀ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች ደንብ ልብስ ተቋማቸው በኢትዮጵያ ቅርንጫፉ ከሚሰራቸው አቅርቦቶች ትልቁ…
Read More