Betkingpremierleague

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘንድሮውን የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ባህርዳር ከነማ ውድድሩን በሁለተኝነት አጠናቋል። የ2015 የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ አሸናፊነት ተጠናቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ64 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ባህርዳር ከነማ ደግሞ በ60 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን በ49 ነጥቦች የውድድር ዓመቱን አጠናቀዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ወይም ፈረሰኞቹ ፕሪምየር ሊጉን ለ31ኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነዋል። የወራጅነት ደረጃዎች ላይ ደግሞ አርባምንጭ እግር ኳስ ክለብ በ34 ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ ክለብ በ18 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ15 ነጥቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርደዋል። የኮኮብ ግብ አግቢነት ደረጃውን የቅዱስ ጊዮርጊሱ እስማኤል አጎሮ በ25 የውድድር ዓመቱ ኮኮብ ግብ አግቢ ሆኖ አጠናቋል።
Read More
ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ጨዋታ የሊጉ መሪ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስን ከኢትዮጵያ ቡና አገናኝቷል። በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። እስማኤል ኦሮ አጎሮ ቅዱስ ጊዮርጊስን ቀዳሚ ያደረገች ጎል ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ከመቻል ጋር እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ተብሏል። ከአራት ቀናት በኋላም ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና፣ አርባምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ፣ ወላይታ ዲቻ ከወልቂጤ ከተማ፣ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ መድህን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ59 ነጥቦች ሲመራ ባህርዳር በ54 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን ደግሞ በ48 ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።…
Read More
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በከፍተኛ ሊግ የምድብ ሀ ዋንጫን አነሳ፡፡ ከሁለት ጨዋታዎች በፊት ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው የምድብ ሀ የከፍተኛ ሊግ ውድድር የመዝጊያ ስነ-ሥርዓት ላይ ዋንጫውን አንስቷል፡፡ ቡድኑ ቀሪ የመርሐ ግብር ጨዋታውን ከቀኑ 6፡00 ላይ ከሰንዳፋ በኬ ጋር በማድረግ 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፎ ነጥቡን 60 ማድረስ ችሏል፡፡ በውድድሩ የመዝጊያ መርሃ ግብር ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመርቻንት እና ኤጀንት ባንኪንግ ዳይሬክተር አቶ ብሌን ኃ/ሚካኤል እና ሌሎች እንግዶች ለሻምፒዮኑ ቡድን እና ለሌሎች ተሸላሚዎች…
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመቻል ተሸነፈ

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐ ግብር መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመቻል ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል። የመቻልን የማሸነፊያ ግብ የቀድሞ የፈረሰኞቹ ተጨዋች ከነዓን ማርክነህ በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ፈረሰኞቹ በዛሬው ጨዋታ ሙሸነፋቸውን ተከትሎ በውድድር አመቱ ሁለተኛ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል። የቀድሞው መከላከያ እግር ኳስ ክለብ የአሁኑ መቻል ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 33 በማድረስ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሽንፈት ያስተናገደው ቅዱስ ጊዮርጊስ በ51 ነጥብ ሊጉን እየመራ ይገኛል። የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሽንፈት ማስተናገዱን ተከትሎ ከተከታዩ ባህርዳር ከተማ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ጠቧል። በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሀዋሳ ከተማ እንዲሁም መቻል ከ ሲዳማ…
Read More
ሻሸመኔ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ወደ ፕሪሜር ሊግ አደገ

ሻሸመኔ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ወደ ፕሪሜር ሊግ አደገ

በሳሙኤል አባተ በምድብ ለ ሀዋሳ ላይ እየተከናወነ በሚገኜው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ውድድር ሻሸመኔ ከነማ ቀሪ 4 ጨዋታ እያለው ወደ ቤቲኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ ማደጉን አረጋግጧል ። በዕለተ ማክሰኞ ሚያዚያ 24 አዲስ አበባ ከነማ በቦዲቲ ከነማ 2ለ1 መሸነፉን ተከትሎ ሻሸመኔ ቀሪ 4 ጨዋታዎች እያሉት በ 47 ነጥብ ፕሪሜር ሊጉን ተቀላቅሏል ። አዲስ አበባ ከነማ በ35 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በቀጣይ ቀሪ 2 ክለቦች ሊጉን ይቀላቀላሉ ። በምድብ ሐ  ሀምበርቾ ዱራሜ በ 42 ነጥብ ገላን ከተማ በ 40 ነጥብ የምድቡ አንደኛ ሁኖ ለማለፍ የሚያደርጉት ፉክክር ይጠበቃል ። በተመሳሳይ በምድብ ሀ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ 50 ነጥብ ምድቡን ሲመራ ቤንቺ ማጅ በ…
Read More