Diasporas

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራዎች 50 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ንግድ ባንክ ለዲያስፖራው ማኀበረሰብ 50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አዘጋጅቼ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል። የባንኩ የብድር አገልግሎቱ ለኢንቨስትመንት፣ ለመኖሪያ ቤትና አውቶሞቢል ግዥ የቀረበ ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ሰሞኑን በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት ፕሬዚደንቱ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን  የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት በአገር ውስጥ ለሚያካሄዱት የቢዝነስ እንቅስቃሴ፣ ለመኖሪያ ቤትና መሰል ፍላጎቶች የ50 ቢሊዮን ብር የብድር አገልገሎት ተመቻችቷል ብለዋል፡፡ የብድር አገልግሎቱ በተያዘው የ2024/25 በጀት ዓመት ተፈጻሚ እንደሚሆንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡ ባንኩ አገልግሎቱን ለማግኘት ጥያቄ ለሚያቀርቡ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ቀልጣፋና ምቹ አሰራር እንደሚተገብርም አቶ አቤ አስታውቀዋል፡፡ ሙሉ ለሙሉ የመንግስት…
Read More
የፌዴራል ቤቶች ኮርፓሬሽን ለዲያስፓራ ኢትዮጵያውያን ቤት መሸጥ ሊጀምር መሆኑን ገለጸ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፓሬሽን ለዲያስፓራ ኢትዮጵያውያን ቤት መሸጥ ሊጀምር መሆኑን ገለጸ

ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ ሀይል እና እቅድ ወደ ስራ መግባቱን የገለጸው የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በሃገር ውስጥ ካለው ነዋሪ ባሻገር በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ኘሮጀክት ለመጀመር ዝግጅት እያደረኩ ነው ብሏል። ስለ ኘሮጀክቱ እና ስለተቋሙ ገለፃ ለማድረግም በኮርፓሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል የተመራ ልዑክ ወደ ብሪታንያ በማምራት በዚያ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የማህበረሰብ አመራሮች ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውንን ተጠቃሚ ለማድረግ በአዲስ መልክ ያቀደውን የቤት ልማት ፕሮጀክት ስኬታማ እንዲሆን ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ተጨማሪ ሀሳበችንና ተሞክሮዎችን መሰብሰቡ ተገልጻል። ከዚሁ ጎን ለጎን በዋና ስራ አስፈፃሚው የሚመራው የልዑካን ቡድኑ በለንደንና አካባቢው በሚገኙ ከሁለተኛ የዓለም ጦርነት…
Read More