NBE

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ማደጉ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ማደጉ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከባንኮች የውጭ ንግድ ግብይት ብቻ በየወሩ 500 ሚሊዮን ዶላር እያገኘች እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ካሳለፍነው ሐምሌ ወር ጀምሮ የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲመራ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምኅረቱ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ የባንኮች የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከወጪ ንግድ ብቻ በወር በአማካይ 500 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል፡፡ ዋና ገዢው አክለውም የባንክ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረበት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ወደ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ማደጉንም ገልጸዋል፡፡ አቶ ማሞ አክለውም ከኹለት ሳምንት በፊት በባንኮች መካከል በተጀመረው የእርስ በርስ የውጭ ምንዛሬ ግብይት ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግብይት እንደተካሄደም ተናግረዋል። የተለያዩ ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት…
Read More
የኢትዮጵያ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫን እንዲያጠቡ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫን እንዲያጠቡ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከውጭ ምንዛሪ ግብይት ጋር በተያያዘ ስለሚፈጸሙ ክፍያዎች የማሻሻያ ፖሊሲ ይፋ አድርጓል:: ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች በየእለቱ የውጭ ምንዛሬ ተመን ይፋ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በዚህም ባንኮች በየእለቱ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የዋጋ ተመን ላይ በመግዣ እና በመሸጫው መካከል ከ10 በላይ ልዩነት ሲታይበት ቆይቷል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫው፤ አዲሱ የምንዛሬ ተመን አሰራር ይፋ መሆኑን ተከትሎ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ ያሉ ሂደቶችን ሲከታተል መቆየቱን አስታውቋል። ብሔራዊ ባንክ የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት በዓለም አቀፍ አሰራር መሰረት መሆን እንዳለበት አመልክቷል። በመሆኑም የውጭ ምንዛሬ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት…
Read More
ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ ከዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ ማድረግ ጀምራለች፡፡ ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች በዲሱን የምንዛሬ ተመን ዛሬ ተግባራዊ ማድረግ ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ማሻሻውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫው የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወስንበት የገበያ ሥርዓት መሸጋገሩን አስታውቋል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ባወጣው የውጭ ምንዛሬ ተመን መሰረት አንድ የአሜሪካ ዶላር በ74.7364 ብር እየተገዛ በ76.2311 እየተሸጠ መሆኑን አስታውቋል። ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊነትን ተከትሎ በምንዛሬ ተመን በአንድ ዶላር ላይ በአማካይ የ18 ብር ጭማሪ ታይቷል። በኢትዮጵያ ንግድ…
Read More
በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

ንግድ ባንክ ባሳለፍነዉ አርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ባጋጠመዉ ችግር 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉና 2.6 ቢሊየን ብር መንቀሳቀሱን አስታውቋል ባንኩ ገንዘብ የወሰዱ ሰዎችን ለመጠየቅና ገንዘቡን ለማስመለስ ግብረሀይል ያቋቋመ ሲሆን በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ገምተዋል፡፡ ቅዳሜ ዕለት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙ ተገልጿል፡፡ ግብረ ሀይሉ ከብሔራዊ ባንክና ከንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት የተካተቱበት ነው የተባለ ሲሆን ዓላማው ደግሞ በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ማስመለስ እና ማጣራት ነው፡፡ ይሁንና ባንኩ በተባለው ሰዓታት ውስጥ የተወሰደበትን የገንዘብ…
Read More
ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለአምስት የውጭ አገር ባንኮች ፍቃድ እንደምትሰጥ ገለጸች

አምስት የውጭ አገር ባንኮች ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው ፈቃድ እንደሚሰጣቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ። አገር በቀል ባንኮች ከወዲሁ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረግ እና ቀድሞ የነበራቸውን ስትራቴጂ መከለስ እንዳለባቸውም ባንኩ አሳስቧል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የገንዘብ ተቋማት ዘርፍ ምክትል ገዥ አቶ ሠለሞን ደስታ እንዳሉት የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማትን ከማጠናከር ጎን ለጎንም የውጭ ባንኮችን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት እየተሰራ ነው። ‹‹ሥራውን አሁን እያጠናቀቅን ነው። አዋጁን የመከለስ ሥራውንም እያጠናቀቅን ነው:: ከለጋሾች አንዳንድ ግብዓቶችን እየጠየቅን ነው። በወራት ዕድሜ ለህዝብ እንደራሴዎች ይቀርባል:: ስለዚህ ስራው እየተፋጠነ ነው” ብለዋል አቶ ሠለሞን። በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት እስከ አምስት ለሚደርሱ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም አቶ ሠለሞን…
Read More