DigitalEthiopia

አሸዋ ቴክኖሎጂ  ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አሸዋ ቴክኖሎጂ ተጨማሪ የአክስዮን ሽያጭ ጀመረ

አክስዮን ገዢዎች  በ500 ሺ ብር  አክስዮን በስድስት አመት ውስጥ ከስድስት ሚልየን ብር በላይ እንደሚያገኙ ተገልጿል። አሸዋ ቴክኖሎጂ በሰው ሃብት አስተዳደር ፣ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ  እና የቢዝነስ  ክንውኖችን ማቀላጠፊያ ሶፍትዌሮችን በማበልጸግ ወደ ስራ የገባ አገር በቀል ድርጅት ነው። የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዳንኤል በቀለ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ግለሰቦች እና ድርጅቶች አክስዮን  ገዝተው ትርፍ የሚጋሩበትን ለሶስት ወራት የሚቆይ የአክስዮን ሽያጭ መጀመሩን ተናግረዋል። የአንድ አክስዮን ዋጋ 2 ሺህ 500 ብር እየሸጠ ያለው አሸዋ ቴክኖሎጂ  ትንሹ አክስዮን 500 ሺህ ብር ሲሆን  ትልቁ አክስዮን ደግሞ 100 ሚልየን ብር እንደሆነ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። የአክስዮን ገዢዎች የገዙትን አክስዮን መጠን 50 በመቶውን ቅድሚያ መክፈል ይጠበቅባቸዋል የተባለ ሲሆን ቀሪ የአክስዮን ድርሻዎችን ደግሞ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

በኢትዮጵያ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት በስፋት ጥቅም ላይ ከዋለ የአገር ዉስጥ እድገት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጨምር ዓለም አቀፍ የሞባይል ግንኙነት ስርዓት ማኅበር አስታውቋል። ይህም የሚሆነው በፈረንጆች 2030 ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ 60 በመቶ ያህሉ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ከሆኑ ነው ያለው ማኅበሩ፤ በተጨማሪም 700 ሺሕ ሰዎችን ከአስከፊ ድህነት እንደሚያወጣና የታክስ ገቢን በ300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምር አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በአንፃራዊነት 99 በመቶ የኔትወርክ ሽፋን ተደራሽነት ቢኖርም፤ የኔትዎርክ ጥራት አስተማማኝ አለመሆን፣ የዲጂታል ስርዓቱ ግንዛቤ ጉድለት፣ የዕምነትና የመረጃ ግላዊነትና ደህንነት ጥያቄ እንዲሁም የግብይቶች በተደጋጋሚ መስተጓጎል የሞባይል ገንዘብ ክፍያን እና አጠቃቀም ላይ እንቅፋት እየሆነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በ2021 የኤሌክትሪክ ኃይል ያላቸው ኢትዮጵያውያን 51…
Read More
ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የቴሌኮም ኩባንያ አሁን ደግሞ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘቱን አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ባንኩ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድን ለሳፋሪ ኮም መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡ ይህም ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ አገር ኩባንያ እንደሚያደርገው የብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን አዲስ ሀላፊነት መስጠቱ ይታወሳል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች…
Read More