digitalmoney

በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የባንኮች የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በባንክ የሚካሄድ አጠቃላይ የገንዘብ ዝውውር ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች ማኅበር "ባካሄድኩት ጥናት አረጋግጫለሁ" ብሏል። በማኅበሩ ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪ ናስር የኑስ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በተለይ ከ2012 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት አንስቶ፣ በይበልጥ ደግሞ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የገንዘብ ዝውውር (ትራንዛክሽን ባንኪንግ) አገልግሎት የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር እየቀነሰ ነው። ለዚህ የገንዘብ ዝውውር መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ያሏቸውን ጉዳዮች የጠቀሱት የምጣኔ ሃብት ተመራማሪው፤ የዜጎች የገቢ ማሽቆልቆል፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ግጭቶችና ጦርነቶች እልባት አለማግኘት፣ የሥራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ችግር እንደሆኑ ዘርዝረዋል። ተመራማሪው ይህንን እያሽቆለቆለ ያለውን የገንዘብ ዝውውር ለማነቃቃት ባንኮች ሊተገብሯቸው ይገባል ካሏቸው የመፍትሔ እርምጃዎች መካከል፤ ባንኮች ለገንዘብ ዝውውር…
Read More
የሳፋሪኮሙ ኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ስራ ጀመረ

የሳፋሪኮሙ ኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ስራ ጀመረ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት የሆነው ኤምፔሳ (M-PESA) ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ፍቃድ ካገኘ ከሦስት ወራት በኋላ ስራ መጀመሩን አስታወውቋል። ኩባንያው ባለፉት ሦስት ወራት አስፈላጊ የሲስተም ፍተሻዎችን እና የቴክኒክ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱንም ገልጿል። ኩባንያው ከዚህ በተጨማሪም ከባንኮች ጋር አብሮ ለመስራት የአጋርነት ስምምነቶች ከመፈራረም ጀምሮ ወኪሎችን መመልመሉን እና ማሰልጠኑንም አስታውቋል። አገልግሎቱን ለማግኘትም የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ደንበኞች የሆኑ ሁሉ የኤምፔሳ አገልግሎትን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል። ደንበኞች የአንድሮይድ (Android) እና የአይኦኤስ (IOS) ስልክ ተጠቃሚዎች በሳፋሪኮም መስመራቸው *733# ላይ በመደወል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተገልጿል። የኤምፔሳ መተግበሪያ በ5 ቋንቋዎች የተዘጋጀ እና የአንድሮይድ ተጠቃሚዎች ከፕሌይስቶር በማውረድ መጠቀም የሚችሉት ሲሆን፤ የአይኦኤስ (IOS) ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ በአፕስቶር…
Read More
ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

በኢትዮጵያ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት በስፋት ጥቅም ላይ ከዋለ የአገር ዉስጥ እድገት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጨምር ዓለም አቀፍ የሞባይል ግንኙነት ስርዓት ማኅበር አስታውቋል። ይህም የሚሆነው በፈረንጆች 2030 ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ 60 በመቶ ያህሉ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ከሆኑ ነው ያለው ማኅበሩ፤ በተጨማሪም 700 ሺሕ ሰዎችን ከአስከፊ ድህነት እንደሚያወጣና የታክስ ገቢን በ300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምር አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በአንፃራዊነት 99 በመቶ የኔትወርክ ሽፋን ተደራሽነት ቢኖርም፤ የኔትዎርክ ጥራት አስተማማኝ አለመሆን፣ የዲጂታል ስርዓቱ ግንዛቤ ጉድለት፣ የዕምነትና የመረጃ ግላዊነትና ደህንነት ጥያቄ እንዲሁም የግብይቶች በተደጋጋሚ መስተጓጎል የሞባይል ገንዘብ ክፍያን እና አጠቃቀም ላይ እንቅፋት እየሆነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በ2021 የኤሌክትሪክ ኃይል ያላቸው ኢትዮጵያውያን 51…
Read More
ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ብሔራዊ ባንክ ለኤምፔሳ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ፈቀድ ሰጠ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የቴሌኮም ኩባንያ አሁን ደግሞ ተጨማሪ ፈቃድ ማግኘቱን አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ፈቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝቷል። የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ባንኩ የዲጅታል ፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድን ለሳፋሪ ኮም መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡ ይህም ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሞባይል የገንዘብ ክፍያ አገልግሎት ፈቃድ ያገኘ የመጀመሪያው የውጭ አገር ኩባንያ እንደሚያደርገው የብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመለክታል፡፡ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን አዲስ ሀላፊነት መስጠቱ ይታወሳል። አምባሳደር ሔኖክ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የውጭ ጉዳዮች…
Read More