24
Sep
ኩባንያው በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለዘመድ አዝማድ የሚልኩትን ገንዘብ (ሪሚታንስ) በማስተላለፍ አገልግሎት ላይ ለመሠማራት ማቀዱን አስታውቋል። ኩባንያው በዘርፉ መሠማራት የፈለገው፣ የውጭ ምንዛሬ ፖሊሲ ለውጡ በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የምንዛሬ ልዩነት ማጥበቡን ተከትሎ ነው ኩባንያው፣ ኬንያና ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሪሚታንስ አስተላላፊነት ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን ከዓለማቀፉ ገንዘብ አስተላላፊ ኩባንያ ዳሃብሺል ጋር ባለፈው ሐምሌ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል። የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት የሆነው ኤምፔሳ (M-PESA) ከአንድ ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ፍቃድ ካገኘ ከሦስት ወራት በኋላ ስራ መጀመሩ አይዘነጋም። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኔትወርክ ማስፋፊያ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር መድቤያለሁ ብሏል፡፡ ተቋሙ አክሎም በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎችበተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ…