Tradeunions

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አባል ማህበራት የሰራተኞች ጥያቄ ካልተመለሱ  ስራ የማቆም አድማና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ሲል አስጠንቅቋል፡፡ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በመንግስት እንዲወሰንና ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ከፍተኛ_ግብር እንዲቀንስ መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ተብሏል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ሰራተኞች ወደ ስራ ማቆም አድማና ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያመሩ እንደሚችሉ ማህበራቱ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የኢትዮጵያን ሰራተኞች ይወክላሉ ከሚባሉት አባላቱ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት አድርጎት በነበረው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ አባላቱ በሰራተኞች ጥቅም ዙሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ማህበራቱ በመግለጫቸው እስካሁን ስናነሳቸው የነበሩ ጥያቄዎቻችን በመንግስት ባለመመለሳቸው ከዚህ በኋላ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ እንዲሁም በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንገደዳለን ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የውጭና ህዝብ…
Read More
በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ማህበራዊ ፍትህ ለማስፈን በሚል ነበር ከ100 ዓመት በፊት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የተቀላቀለችው፡፡ ከአፍሪካ በብቸኝነት ድርጅቱን የተቀላቀለችው ኢትዮጵያ 100ኛ ዓመቱን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመራሮች፣ አሰሪዎች፣ የሰራተኛ ማህበራት አመራሮች እና ባለሙያዎች በተገኙበት በማክበር ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ በዓል ላይ ተገኝነተው ንግግር ያደረጉት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ፋፋን ርዋንይንዶ ካይራንግዋ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከ23ቱ የአይኤልኦ ስምንቶች መካከል ስምንቱን ማጽደቋን አድንቀዋል፡፡ ዳይሬክተሯ አክለውም ኢትዮጵያ የሰራተኞችን ደህንነት ለማሻሻል በርካታ የወሰደቻቸው እርምጃዎች ቢኖሩም ለሰራተኞች የዝቅተኛ ደመወዝ እርከን ጣሪያን እንድትወስን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ እንዳሉት ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የሰራተኞች ድርጅት ከተቀላቀለች 100 ዓመት የሞላት…
Read More