Tradeunions

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ  ሠራተኞች  የሥራ ማቆም አድማ ላይ መቱ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ  ሠራተኞች  የሥራ ማቆም አድማ ላይ መቱ

400 ያህል የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የጥሪ ማዕከል ሠራተኞች "አይሶን ኤክስፔሪያንስ" የተሰኘ ወኪል ድርጅት ይፈጸምብናል ባሉት የአስተዳደር በደል ሳቢያ ላለፉት 2 ቀናት የሥራ ማቆም አድማ ላይ መሆናቸውን ዋዜማ ዘግቧል። ሠራተኞቹ በዋናነት የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉት፤ በወኪል ድርጅቱ በኩል የሚከፈላቸው ደመወዝ ዝቅተኛ በመሆኑ እንደሆነ ታውቋል። ወኪል ድርጅቱ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ሠራተኞችን በተጠና መልኩ ከሥራ እንዲሰናበቱ እያደረገ እንደሆነና ባለፈው ዓመት መጋቢት ወር ብቻ 80 ያህል ሠራተኞችን ሕጋዊነቱን ባልተከተለ መንገድ እንዳሰናበተ ተነግሯል ። ተመሳሳይ የሥራ ዓይነት ለሚሠሩ ሠራተኞች፣ ቋንቋንና ማንነትን መሠረት ያደረገ ሕገወጥ የደመወዝ ልዩነትና አድሎ እንዳለና ድርጅቱ ችግሩን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ተጠይቆ ሊያስተካክል እንዳልቻለ የድርጅቱ ሰራተኛ ማኅበር አስታውቋል ። የድርጅቱ እህት ኩባንያ የሆነው ሳፋሪኮም…
Read More
በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አባል ማህበራት የሰራተኞች ጥያቄ ካልተመለሱ  ስራ የማቆም አድማና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ሲል አስጠንቅቋል፡፡ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በመንግስት እንዲወሰንና ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ከፍተኛ_ግብር እንዲቀንስ መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ተብሏል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ሰራተኞች ወደ ስራ ማቆም አድማና ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያመሩ እንደሚችሉ ማህበራቱ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የኢትዮጵያን ሰራተኞች ይወክላሉ ከሚባሉት አባላቱ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት አድርጎት በነበረው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ አባላቱ በሰራተኞች ጥቅም ዙሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ማህበራቱ በመግለጫቸው እስካሁን ስናነሳቸው የነበሩ ጥያቄዎቻችን በመንግስት ባለመመለሳቸው ከዚህ በኋላ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ እንዲሁም በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንገደዳለን ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የውጭና ህዝብ…
Read More
በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ማህበራዊ ፍትህ ለማስፈን በሚል ነበር ከ100 ዓመት በፊት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የተቀላቀለችው፡፡ ከአፍሪካ በብቸኝነት ድርጅቱን የተቀላቀለችው ኢትዮጵያ 100ኛ ዓመቱን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመራሮች፣ አሰሪዎች፣ የሰራተኛ ማህበራት አመራሮች እና ባለሙያዎች በተገኙበት በማክበር ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ በዓል ላይ ተገኝነተው ንግግር ያደረጉት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ፋፋን ርዋንይንዶ ካይራንግዋ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከ23ቱ የአይኤልኦ ስምንቶች መካከል ስምንቱን ማጽደቋን አድንቀዋል፡፡ ዳይሬክተሯ አክለውም ኢትዮጵያ የሰራተኞችን ደህንነት ለማሻሻል በርካታ የወሰደቻቸው እርምጃዎች ቢኖሩም ለሰራተኞች የዝቅተኛ ደመወዝ እርከን ጣሪያን እንድትወስን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ እንዳሉት ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የሰራተኞች ድርጅት ከተቀላቀለች 100 ዓመት የሞላት…
Read More