ILO

ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

ካሳሁን ፎሎ የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለቀጣዮቹ 3 ዓመታት የዓለም ሥራ ድርጅት አስተዳድር አባል ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው የዓለም ሥራ ድርጅት (ILO) 112ኛ ጉባኤ ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደው ስብሰባ ለቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚቆጣጠሩና የሚያስተዳድሩ አካላትን ከሠራተኞች ፣ከመንግሥታትና ከአሠሪዎች መካከል ለመምረጥ ባደረገው እንቅስቃሴ  ካሳሁን ፎሎ  የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ የዓለም ሥራ ድርጅት የሚያስተዳድረው አካል አባል በመሆን መመረጣቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ 112ኛ ጉባኤ ቅዳሜ ግንቦት 30 ቀን 2016 ባካሄደው ስብሰባው የዓለም ሥራ ድርጅትን በበላይነት የሚያስተዳድር (Governing Body)  ምክትል አባል ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን አንዷ አድርጎ መርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ከተወዳደሩት ሰባት ሀገራት…
Read More
ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮያውያንን ወደ ሀገራቸው እመልሳለሁ ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ “በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለስ ሦስተኛ ምዕራፍ በሁለት ሳምንት ውስጥ ይጀምራል” ብለዋል። በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኘው ኢትዮያውያንን ለመመለስ የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመመለስ በተዘጋጀው ዕቅድ ላይ መክሯል። የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፤ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ በብሔራዊ ኮሚቴው ውስጥ የታቀፉት የፌዴራል ተቋማት እና የክልሎችን የጋራ ቅንጅት ይጠይቃል ብለዋል። ከወዲሁ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተሟላ ሁኔታ በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አምባሳደር ብርቱካን ተናግረዋል። አምባሳደር…
Read More
በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

በኢትዮጵያ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት ጠየቀ

ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ማህበራዊ ፍትህ ለማስፈን በሚል ነበር ከ100 ዓመት በፊት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የተቀላቀለችው፡፡ ከአፍሪካ በብቸኝነት ድርጅቱን የተቀላቀለችው ኢትዮጵያ 100ኛ ዓመቱን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመራሮች፣ አሰሪዎች፣ የሰራተኛ ማህበራት አመራሮች እና ባለሙያዎች በተገኙበት በማክበር ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ በዓል ላይ ተገኝነተው ንግግር ያደረጉት ዓለም አቀፉ የሰራተኞች ድርጅት የአፍሪካ ዳይሬክተር ፋፋን ርዋንይንዶ ካይራንግዋ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከ23ቱ የአይኤልኦ ስምንቶች መካከል ስምንቱን ማጽደቋን አድንቀዋል፡፡ ዳይሬክተሯ አክለውም ኢትዮጵያ የሰራተኞችን ደህንነት ለማሻሻል በርካታ የወሰደቻቸው እርምጃዎች ቢኖሩም ለሰራተኞች የዝቅተኛ ደመወዝ እርከን ጣሪያን እንድትወስን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ እንዳሉት ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የሰራተኞች ድርጅት ከተቀላቀለች 100 ዓመት የሞላት…
Read More