CETU

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የስራ ማቆም አድማ ሊደረግ እንደሚችል ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አባል ማህበራት የሰራተኞች ጥያቄ ካልተመለሱ  ስራ የማቆም አድማና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ሲል አስጠንቅቋል፡፡ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በመንግስት እንዲወሰንና ከደመወዝ ላይ የሚቆረጠው ከፍተኛ_ግብር እንዲቀንስ መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠየቅም እስካሁን ምላሽ አልሰጠም ተብሏል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ሰራተኞች ወደ ስራ ማቆም አድማና ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያመሩ እንደሚችሉ ማህበራቱ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የኢትዮጵያን ሰራተኞች ይወክላሉ ከሚባሉት አባላቱ ጋር ባሳለፍነው ሳምንት አድርጎት በነበረው ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ አባላቱ በሰራተኞች ጥቅም ዙሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ማህበራቱ በመግለጫቸው እስካሁን ስናነሳቸው የነበሩ ጥያቄዎቻችን በመንግስት ባለመመለሳቸው ከዚህ በኋላ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ እንዲሁም በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ እንገደዳለን ማለታቸውን የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን የውጭና ህዝብ…
Read More
አቶ ካሳሁን ፎሎ በድጋሚ የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

አቶ ካሳሁን ፎሎ በድጋሚ የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሂዷል፡፡ (ኢሠማኮ) በአዲስ አበባ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ኮንፌዴሬሽኑን በቀጣዮቹ 5 ዓመታት አመራሮችን መርጧል፡፡ በዚህም ላለፉት ዓመታት ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋ፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ አቶ ድሪብሳ ለገሰ እና አቶ አብዱልሐኪም ሙሰማ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ እንደመረጠም ሰምተናል፡፡ አቶ ካሳሁን ከምርጫው በኋላ ባደረጉት ንግግር በሀላፊነት የሚቀጥሉት ለመጨረሻ ጊዜ እንደሆነ በጉባኤው ላይ ገልጸዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ አክለውም መንግሥት ለሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን በድጋሚ ጠይቀዋል። ካሳሁን፣ መንግሥት ሠራተኞች በሚከፍሉት የደመወዝ ገቢ ግብር ላይ ቅናሽ እንዲያደርግ ኢሠማኮ በተደጋጋሚ ሲጠይቀው ለነበረው ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥም አሳስበዋል። በዓለማቀፍና የአገር ውስጥ ችግሮች ሳቢያ ሠራተኞች የኑሮ ውድነቱን ሊቋቋሙት ከሚችሉት በላይ…
Read More
ኢሰማኮ ለሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ ጠየቀ

ኢሰማኮ ለሰራተኞች የሥራ ግብር እንዲቀነስ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ እንዳሉት በቋሚ ደመወዝ ለሚተዳደሩ ሰራተኞች የሥራ ግብር መቀነስን ጨምሮ ሌሎች የማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድን በደብዳቤ መጠየቃቸውን ተናግረዋል። የኮንፌደሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ካሣሁን ፎሎ እንደገለጹት ከብር የመግዛት አቅም መዳከም ጋር ተያይዞ ቋሚ ደመወዝ የሚያገኙ ሰራተኞች ለከፍተኛ የኑሮ ውድነት መዳረጋቸውን ገልጸዋል። "በተለይም ዝቅተኛ ገቢ የሚያገኘው ሰራተኛ ቀን ቀን እየሠራ ማታ ማታ ሆቴሎች ላይ ፍርፋሪ እየለመነ እያደረ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የኑሮ ጫናው በተለይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ተቀጥረው በሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። አክለውም ከዚህ በፊት በሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ዙርያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ ጋር ተደጋጋሚ  ውይይቶች መደረጋቸውን አስታውሰው ነገር ግን እነዚህ ውይይቶች ውጤት…
Read More
በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

በውጭ ሀገራት የተቀጠሩ ኢትዮጵያዊያንን ደህንነት ለማስከበር ያለመ ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽንና የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመዋል፡፡ ስምምነቱ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ከኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገናኝ ኤጀንሲዎች አሠሪ ፌዴሬሽን በውጭ ሀገር በሥራ የሚሰማሩ ዜጎችን መብት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ ነው፡፡ በስምምነቱ ወቅት የፌዴሬሽኑ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት ፣የዓለም ሥራ ድርጅት ተወካይ እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ በፊርማው ሥነ-ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኮንፌዴሬሽኑ በሀገር ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ ሠራተኞች መብቶች እንዲከበሩ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ በተጨማሪም በውጭ ሀገራት ተቀጥረው የሚሠሩ ኢትዮጵያዊን መብታቸው ተጠብቆ እዲሠሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ…
Read More