WorldBank

ኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከአይኤምኤፍ አገኘች

ኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከአይኤምኤፍ አገኘች

ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 251 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ብድር እንደሚለቅ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ እንዳስታወቀው ብድሩን ለመልቀቅ ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ከስምምነት ላይ ደርሷል። ድርጅቱ ብድሩን ለማጽደቅ የተስማማው፣ የድርጅቱ የባለሙያዎች ቡድን ከኅዳር 3 እስከ 17 በአዲስ አበባ ተገኝቶ ኹለተኛውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ግምገማ ማድረጉን ተከትሎ ነው። የድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ፣ የብድር መልቀቅ ስምምነቱን በቀጣይ ሳምንታት ውስጥ እንደሚያጸድቀውና ወደፊት የኢኮኖሚ ማሻሻያ ግምገማዎች በየስድስት ወሩ እንደሚካሄዱ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቀረፈና በመደበኛውና በትይዩ የውጭ ሀገራት መገበያያ ምንዛሬዎች መካከል ያለው ልዩነት ከ10 በመቶ በታች መውረዱን የጠቀሰው ድርጅቱ፣ መንግሥት ጥብቅ የገንዘብና ፊስካል ፖሊስ እንዲቀጥል አሳስቧል። ኢትዮጵያ ካሳለፍነው ሐምሌ ወር ጀምሮ በአይኤምኤፍ እና…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ16 ቢሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ሰጠ

የዓለም ባንክ የዳይሬክቶች ቦርድ በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ውስጥ ለኢትዮጵያ የ16 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ብድር እና እርዳታ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ የዓለም ባንክ በድረ ገጹ ባወጣው መግለጫው የገንዘብ ድጋፍና ብድሩ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ ለመደገፍ የሚውል መሆኑን አስታውቋል። በዚህ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ካጸደቀው ገንዘብ ውስጥ 1 ቢሊዮን ዶላር ቀጥተኛ ድጋፍ መሆኑን የገለጸው ባንኩ፤ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ የተራዘመ ብድር ነው ብሏል። የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ እያከናወነችው ያለችውን ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለመደገፍ በርካታ የድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት 1 ቢሊዮን ዶላር የቀጥታ እርዳታ ሲሆን 500 ሚሊዮን ዶላር የእዳ ክፍያ ማራዘሚያ እንዲሁም 320 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ትብብር በሚል…
Read More
ኢትዮጵያ ከብድር እና እርዳታ ከአራት ቢሊዮን በላይ ዶላር ማግኘቷን አስታወቀች

ኢትዮጵያ ከብድር እና እርዳታ ከአራት ቢሊዮን በላይ ዶላር ማግኘቷን አስታወቀች

የገንዘብ ሚኒስቴር በበጀት ዓመቱ የዘጠኝ ወራት እቅዱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሚኒስቴሩ ባቀረበው የፋይናንስ ሪፖርቱ ላይ እንዳለው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከብድር እና እርዳታ 4 ነትብ 5 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ብሏል፡፡ ከተገኘው ከዚህ ውስጥ 54 በመቶው ዕርዳታ ነው የተባለ ሲሆን 849 ሚሊዮን ዶላር በብድር የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ከተገኘው ገቢ ውስጥም የዓለም ባንክ አንድ ቢሊዮን ዶላር ወደ ኢትዮጵያ ፈሰስ አድርጓል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ጋር መልካም ግንኙነት እንዳላትም አስታውቃለች፡፡ ከሀገር ውስጥ ገቢ ለመሰብሰብ 356.5 ቢሊዮን ብር ለመሰብስብ ታቅዶ 338 ቢሊዮን ብር ገቢ እንደተሰበሰበም ተገልጿል፡፡ እንዲሁም ወደ ግል ይዞታ ከተዛወሩ የመንግስት ድርጅቶች በዘጠኝ ወር ውስጥ ከወቅታዊ እና ከውዝፍ ዕዳ ብር…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ከ850 ሚሊዮን ዶላር በላይ እርዳታ ሰጠ

ኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊዮን ዶላር ወይም የ97 ቢሊዮን ብር እርዳታ እና በድር ስምምነት መፈራረማቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ተወካይ የሆኑት ኦስማን ዲዮን ተፈራርመዋል ተብሏል፡፡ ከዓለም ባንክ ከተገኘው የገንዘብ ድጋፍ ውስጥ 850 ሚሊዮን ዶላር ያህሉ በእርዳታ ለኢትዮጵያ የተለያዩ ስራዎችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ቀሪው ገንዘብ ደግሞ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት እና ለማከናወን በሚል በብድር መልኩ ከባንኩ እንደተሰጠ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ በእርዳታ ከተሰጠው ገንዘብ ውስጥ 500 ሚሊዮን ዶላሩ ለገጠር አካባቢዎች የምግብ ዋስትና፣ የአየር ንብረት ለውጥ ስራዎችን ለመደገፍ፣ 82 ዶላሩ ደግሞ በከተማ አካባቢዎች ምግብ ዋስትና ስራዎችን ለማረጋገጥ…
Read More
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በማካሄድ ላይ ላለችው የኢኮኖሚ ሪፎርም እና ችግር ላይ የሚገኘውን የፋይናንስ ሁኔታዋን ለመቅረፍ ያግዛት ዘንድ ከአለም አቀፉ ገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር እየተነጋገረች መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። በሀገሪቱ የሚታየውን አመታዊ የበጀት ጉድለቷን ለሞሙላት ያግዛት ዘንድ በልዩ ሁኔታ ከአይኤም ኤፍ ብድር መጠየቋን ዘገባው አመላክቷል። የመንግሥት ባለስለጣናት  ባለፈው ሳምንት ከአለም አቀፍ ቦንድ ገዢዎች ጋር በነበራቸው ስብሰባ በቀጣዩ የፈረንጆች አመት 2024 መጀመሪያ ሶስት ወራት ከአይ ኤም ኤፍ ጋር የብድር ስምምነት ላይ እደርሳለን ብለው እንድደሚያምኑ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ያለት የገቢ ንግድ ማስኬጃ የውጭ ምንዛሬ መጠን ክምችት ዜሮ ነጥብ ሁለት በመቶ ብቻ እንደሆነ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ኢትዮጵያ የገጠማትን የበጀት ጉድለት ለመሙላት…
Read More
የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የዓለም ባንክ ለኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ 730 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ

የገንዘብ ሚኒስቴርና የዓለም ባንክ ለአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ኮሪደር ፕሮጀክት (በኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር ፕሮጀክት) የ730 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት መፈራረማቸው ይፋ ተደርጓል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያን 90 በመቶ የባህር ንግድን የሚይዘው ስትራቴጂካዊው ከአዲስ አበባ-ጅቡቲ ኮሪደር ጋር በተሳሰረ መልኩ የኢትዮጵያን የሎጅስቲክስና የትስስር አቅም እንደሚያጎለብት ተጠቁሟል። በስምምነቱ መሰረት ለሜኦሶ-ድሬዳዋ መንገድ ግንባታ የፋይናንስ ድጋፍ የሚደረግ ሲሆን፤ ግንባታው የትራንስፖርት አቅምና ብቃት የሚጨምር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል። መንገዱ በሚገነባባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች የጤና፣ ውሃና ትምህርት አገልግሎት ተደራሽነት ጨምሮ ሌሎች መሰረተ ልማቶች ድጋፍ እንደሚደረግም ተመላክቷል። ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሺዬቲቭ አካልና የቀጣናዊ ትብብር ማዕቀፍ እንደሆነ ያመለከተው ሚኒስቴሩ፤ ማዕቀፉ አካባቢውን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ፋይዳም እንዳለው ተጠቅሷል። ስምምነቱን የተፈራረሙትም የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ…
Read More
ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ 400 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ

ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ 400 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ

ኢትዮጵያና የአለም ባንክ ለሰው ሀብት ልማት አገልግሎት የሚውል የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በበይነ መረብ በተካሄደ ሥነ-ስርዓት ተፈራርመዋል፡፡ በስምምነቱ ከተፈረመው 400 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 350 ሚሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ ሲሆን 50 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ብድር መሆኑ ታውቋል፡፡ የፋይናንስ ድጋፉ ለሰው ሀብት ልማት ማለትም የትምህርትን ጥራትንና ውጤታማነትን ለማሻሻልና የስርዓተ ምግብን አገልግሎት ለማጎልበት የሚውል ሲሆን፤ ከአገልግሎቱም በመላ አገሪቱ የሚገኙ ልጃገረዶችና ታዳጊ ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሰው ሀብት ልማት አገልግሎቱ በግጭትና ድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን የሚያካትት ሲሆን፤ የማህበራዊ አገልግሎቶች አሰጣጥን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈንም አስተዋጽዖ እንዳለው ተነግሯል፡፡ የፋይናንስ ድጋፉ ውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋጋጥ የሚያግዝ ከመሆኑም በላይ በተመረጡ ወረዳዎች የስርዓተ ምግብ አገልግሎትን…
Read More
ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

ኢትዮጵያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር እንዲሰጣት ጠየቀች

የኢትዮጵያ መንግስት ለሁለተኛው አገር በቀል የኢኮኖሚ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ 12 ቢሊዮን ዶላር ብድር ጠይቋል፡፡ ብድሩ እና እርዳታው የተጠየቀው የዓለም የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ፣ ዓለም ባንክና ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ዕዳ መልሶ ከማሸጋሸግ ለማግኘት እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ ለሪፖርተር እንዳሉት ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከአሜሪካ፣ ፈረንሣይና ሌሎች ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት መልካም መሆኑ ብድሩ ሊገኝ ይችላል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲስተካከል ጠይቃለች ያሉት አማካሪው ብድሩ ድርድር ከተደረገበት በኋላ ይለቀቃል የሚል ተስፋ መኖሩንም ጠቅሰዋል፡፡ የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ገደብ እ.ኤ.አ. በጁላይ ወር መጨረሻ ላይ ያነሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ፣ ይህም ገንዘቡን ለማግኘት ጥሩ እርምጃ ይሆናልም ተብሏል፡፡ 12 ቢሊዮን…
Read More
የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ። ኢትዮጵያ ከአገር ውስጥ ባንኮች የተበደረችውን ሳይጨምር ከውጭ አበዳሪ ምንጮች ተበድራ ያልመለሰችው የዕዳ መጠን 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚንስቴር አስታውቋል። እንደ ሚኒስቴሩ ሪፖርት ከሆነ ኢትዮጵያ ካለባት 28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ውስጥ 54 በመቶ የተገኘው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት ባንክ ነው፡፡ 46 በመቶው ደግሞ ከቻይና እና ከሌሎች ውጭ የግል አበዳሪ ተቋማት የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ባለባት ከፍተኛ የውጭ ዕዳ ብድር ምክንያትም በዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት ምደባ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ ተመድባለች። በተያያዘ ዜና ኢትዮጵያ ከሶስት ዓመት በፊት የቡድን 20 አገሮች የዕዳ ጫናን ለማቅለል ባዘጋጁት የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሥርዓት ለመጠቀም…
Read More
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ እን አይኤምኤፍ ጋር ስታደርገው የነበረው ውይይት ተጠናቋል። የኢትዮጵያ የፋይናንስ ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘባ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ሃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ለአንድ ሳምንት ሲያደርግ የነበረውን ውይይት አጠናቅቋል፡፡ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሽ በቀለ በትዊተር ገጻቸው እንዳስታወቁት በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና በብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተመራው ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ዳይሬክተሮች ጋር ሲያደርግ የነበረው ውይይት ተጠናቋል፡፡ የፋይናንስ ልዑኩ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይ ኤም ኤፍ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እና ልዑካቸው ጋር ምክክር ማድረጋቸውን እና ለአንድ ሳምንት የቆየውን ውይይት መጠናቀቁን አንስተዋል፡፡ የተደረገው ውይይት ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የልማትና ሰብዓዊ  ድጋፍ ለማግኘት…
Read More