US

አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

አሜሪካንን ጨምሮ ከ25 በላይ ሀገራት በትግራይ ያለው አለመረጋጋት አሳስቦናል አሉ

በትግራይ ክልል በጊዜያዊ አስተዳድሩ እና በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ቡድን መካከል ግጭት መከሰቱን ተከትሎ የመፈንቅለ መንግስት እየተፈጸመ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ጌታቸው ረዳ በመቀሌ እና አዲ አበባ በሰጧቸው መግለጫዎች ላይ እንዳሉት የህወሃት አንዱ ክንፍ በጊዜያዊ አስተዳድሩ ላይ አመራሮችን መሾም፣ ማህተም መቀማት፣ ቢሮዎችን መቆጣጠር እና ሌሎች ህጋዊ ያልሆኑ ስራዎችን እያካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ በትግራይ ክልል አለመረጋጋት የተፈጠረ ሲሆን በክልሉ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አይለዋል፡፡ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ከ20 በላይ ሀገራትም በትግራይ ክልል ያለው ሁኔታ እንዳሳሰባቸው ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ ገልጸዋል፡፡ የጋራ መግለጫውን ካወጡ ሀገራት መካከል አሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ጀርመን፣ፈረንሳይ፣ ስዊድን፣ ቤልጂየም እና…
Read More
አሜሪካ በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት አሳስቦኛል አለች

አሜሪካ በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት አሳስቦኛል አለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር በስልክ መወያየታቸው ተገልጿል። “በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ያሉ የእርስ በርስ ግጭቶች እልባት እንዲያገኙ የፖለቲካ ውይይት ወሳኝነት አለው” ሲሉ አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚኒስትር አብይ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት ወቅት መናገራቸው የመስሪያ ቤታቸው መግለጫ አመላክቷል። አሜሪካ “በአማራ ክልል በመካሄድ ላይ ያለው ግጭት ያሳስባታል” ሲሉ መናገራቸውን በመግለጫው ላይ ተገልጿል። አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ጋር በስልክ ያወሩት በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ዙሪያ እንደነበር ጸ/ቤታቸው ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። አንቶኒ ብሊንከን “ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲደረግ ለምታደርገው ጥረት ሀገራቸው እገዛ ለማድረግ ዝግጁ ናት” ሲሉ መናገራቸውን መግለጫው ጠቁሟል። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር…
Read More
በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበትና በንፁኃን ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንዲቆም አሜሪካ አሳሰበች

በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተመድ ጉባዔ ጎን ለጎን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ሞሊ ፊ ከውይይቱ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ኃይል የበዛበት የመንግሥት ምላሽና ንፁኃን ላይ ያነጣጠረ የታጣቂዎች ጥቃት እንዲቆም አሳስበዋል። ረዳት ሚኒስትሯ ከሁለት ዓመታት በፊት የተካሄደውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሳካ ሁኔታ እንዲፈጸም፣ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር በመሆን ያለ ማቋረጥ ውትወታ እናደርጋለንም ብለዋል። በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ያለውን ግጭት በተመለከተ ያለንን ሥጋት በመግለጽ እንዲቆም በግል በሚደረግ ውይይትና በይፋ በሚኖሩ መግለጫዎች እየጠየቁ መሆኑን አስታውቀዋል። ታጣቂዎች በንፁኃንና በመንግሥት መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እያደረሱ መሆኑን የገለጹት ሞሊ ፊ የመንግሥት…
Read More
የድቪ 2026 ማመልከቻ ከአንድ ሳምንት በኋላ ይጀመራል

የድቪ 2026 ማመልከቻ ከአንድ ሳምንት በኋላ ይጀመራል

የዓለማችን ልዕለ ሀያል የሆነችው አሜሪካ ከፈረንጆቹ 1995 ዓመት ጀምሮ በድቪ ሎተሪ አማካኝነት ወደ ሀገሯ በመውሰድ ለይ ትገኛለች፡፡ ኢትዮጵያ ለዚህ እድል ከተፈቀደላቸው ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን በየዓመቱ በአማካኝ ከ4 ሺህ እስከ 5 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ወደ አሜሪካ ያቀናሉ፡፡ የድቪ 2024 እድለኛ ኢትዮጵያዊን የቪዛ ማመልከቻቸው ከጥቂት ቀናት በኋላ የሚያበቃ ሲሆን የድቪ 2025 እድለኞች ደግሞ ከያዝነው መስከረም ወር መጠናቀቅ በኋላ ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የቪዛ ጥያቄያቸውን ማቅረብ ይጀምራሉ፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም የድቪ 2026 የማመልከቻ ጊዜ ከአንድ ሳምንት በኋላ የሚጀመር ሲሆን ለአንድ ወር እንደሚቆይ የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት አስታውቋል፡፡ የማመልከቻ ጊዜው ከመስከረም 21 ቀን እስከ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት 30 ቀናት ይቆያል የተባለ ሲሆን…
Read More
አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

አሜሪካ በአማራ እና ኦሮሚያ ተማሪዎችን እና ንጹሃን ዜጎችን ማገት እንዲቆም ጠየቀች

ባሳለፍነው ሳምንት ከደባርቅ ዩንቨርሲቲ ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመጓዝ ላይ የነበሩ ተማሪዎች መታገታቸው ይታወሳል፡፡ እገታው የተፈጸመው ለአዲስ አበባ ከተማ ትንሽ ሲቀራቸው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረ ጉራቻ ከተማ አቅራቢያ በታጣቂዎች እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾም ነበር፡፡ የፌደራል መንግስትም ሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግስት እስካሁን ስለ ጉዳዩ በይፋ እስካሁን ያሉት ነገር ባይኖርም የታጋች ተማሪዎች ቤተሰቦች ግን ልጆቻቸው በታጣቂዎች እንደታገቱባቸው ለተለያዩ ብዙሃን መገናኛዎች ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኢምባሲ በጉዳዩ ዙሪያ በወጣው መግለጫ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የተራዘሙ ግጭቶች የህግ የበላይነት እንዳይከበር ምክንያት ሆነዋል ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ላይ ገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት እና ከዚህ በፊት የተፈጸሙ ተከታታይ እገታዎች ወንጀለኞችን እንዳይጠየቁ ማድረጉን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር አረቪን ማሲንጋ መናገራቸውን…
Read More
አሜሪካ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠየቀች

አሜሪካ በኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች ወደ ድርድር እንዲመጡ ጠየቀች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ በአዲስ አበባ መርካቶ አካባቢ የሚገኘውን የአሜሪካ ግቢ ጎብኝተዋል። አምባሳደሩ በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት የአሜሪካ ግቢ ከ87 አመት በፊት ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ከሞት ማምለጫ መሆኑን አውስተዋል። የካቲት 12 1929 ዓ.ም ፋሺስት ጣሊያን በአዲስ አበባ ለሶስት ቀናት ጭፍጨፋ ሲፈጽም አሜሪካዊው ዲፕሎማት ኮርኔልስ ቫን ኤንገርት ከ750 በላይ ኢትዮጵያውያን በኤምባሲው ውስጥ እንዲደደበቁ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። ኢትዮጵያውያን ከ87 አመት የሰውነት ክብራቸው ተጥሶ በህይወት የመኖር መብታቸው ሲነጠቅ ታይቷል ያሉት አምባሳደሩ የሞራል ልዕልና እና ሰብአዊነት ካላቸው ኮርኔልስ ቫን ኤንገርት ልንማር ይገባል ሲሉም ተደምጠዋል። ከ87 አመት በኋላም በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች ሀገራት የሰው ልጆች ክብር እና በህይወት የመኖር መብት በታጣቂዎች፣ ዘራፊ ቡድኖች እንዲሁም በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች መጣሳቸው…
Read More
ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በአሜሪካ የሚኖሩ ተጠርጣሪ ኢትዮጵያዊያን ተላልፈው እንዲሰጧት ጠየቀች

ኢትዮጵያ በወንጀል የምትፈልጋቸውን ሰዎች አሜሪካ አሳልፋ እንድትሰጣት ጥያቄ አቅርባለች፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ  ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያይተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአሜሪካው ኤፍ.ቢ.አይ (FBI) ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር አምባሳደሩ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ ኮሚሽነሩ በውይያታቸው ወቅት ጠይቀዋል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ በተለይም በአሜሪካን ሀገር እየኖሩ የሀገሪቱን ሰላም እያወኩ ነው በሚል የምትጠረጥራቸውን ሰዎች ተላልፈው እንዲሰጧት ለአምባሳደሩ ጥያቄ እንዳቀረቡም ተገልጿል፡፡ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በአሜሪካን መንግሥት የሚፈለጉ ወንጀለኞችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አሳልፎ በመስጠት ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ተብሏል፡፡ አምባሳደሩ አክለውም ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተመሳሳይ ድጋፎችን እንድታደርግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል ሲል የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ…
Read More
አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

አሜሪካ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲመረመር ጠየቀች

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ባሳለፍነው ሳምንት ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በኢምባሲው ማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ባወጡት መግለጫ በመርዓዊ ከተማ የተፈጸመው የንጹሃን ዜጎች ግድያ እንደሚያሳስባቸው፣ ጉዳዩ በገለልተኛ አካል እንዲመረመር ጠይቀዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ እና ኦሮሚያ…
Read More

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጦርነት 350 ሺህ ሰዎች መገደላቸውን ገለጸች

አሜሪካ ኢትዮጵያን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገርነት ዝርዝር ውስጥ ሰርዛለች። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገር ዝርዝር ውስጥ የመዘገበቻት። ይህን ተከትሎም ዋሽንግተን ለኢትዮጵያ ታደርጋቸው የነበሩ የልማት ስራዎች ድጋፎችን አቋርጣ ቆይታለች። እንደ ፎሬይን ፖሊሲ ዘገባ ከሆነ አሜሪካ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጸምባት ሀገር አይደለችም የሚል አቋም ላይ ደርሳለች። በኮሮና ቫይረስ፣ በጦርነት እና በዓለም አቀፍ ንግድ መቀዛቀዝ ምክንያቶች ኢትዮጵያ እንደ ሌሎች ሀገራት የብድር መክፈያ ጊዜ ሽግሽግ እንዲደረግ አስቀድማ ጠይቃ ነበር። ይሁንና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በጣለችው እገዳ ምክንያት ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለብዙ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ያደረጉትን የገንዘብ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ማድረግ…
Read More
የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ። ኢትዮጵያ ከአገር ውስጥ ባንኮች የተበደረችውን ሳይጨምር ከውጭ አበዳሪ ምንጮች ተበድራ ያልመለሰችው የዕዳ መጠን 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚንስቴር አስታውቋል። እንደ ሚኒስቴሩ ሪፖርት ከሆነ ኢትዮጵያ ካለባት 28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ውስጥ 54 በመቶ የተገኘው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት ባንክ ነው፡፡ 46 በመቶው ደግሞ ከቻይና እና ከሌሎች ውጭ የግል አበዳሪ ተቋማት የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ባለባት ከፍተኛ የውጭ ዕዳ ብድር ምክንያትም በዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት ምደባ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ ተመድባለች። በተያያዘ ዜና ኢትዮጵያ ከሶስት ዓመት በፊት የቡድን 20 አገሮች የዕዳ ጫናን ለማቅለል ባዘጋጁት የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሥርዓት ለመጠቀም…
Read More