01
Aug
በተሻሻለው የትራምፕ ታሪፍ ኢትዮጵያ ቀድሞ በተጣለባት ዝቅተኛው 10 ፐርሰንት ታሪፍ እንድትቀጥል ተደርጓል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለአሥርተ ዓመታት የቆዩትን የዓለም ንግድ አሠራሮች ለመለወጥ በሚያደርጉት ጥረት ከሰባ በላይ አገራት ላይ አዲስና የተቀየረ የንግድ ቀረጥ ተግባራዊ ሊያደርጉ መሆኑን አስታወቀዋል። ኢትዮጵያ በአሜሪካ የተጣለባትን የ10 በመቶ ታሪፍ የተቀበለች ሲሆን ታሪፉ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እንደሚያሳድግላት አስታውቃለች። ትናንት በተፈረመው የአስፈጻሚ ትዕዛዝ መሰረት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአገሪቱን የንግድ ጉድለት ከዋነኛ አጋሮች ጋር ለመቀነስ ታስቦ የተደረገ ነው በማለት የገለፁ ሲሆን፣ በዚህም እስከ 41 በመቶ የሚደርስ አዲስ የገቢ ምርቶች ላይ የሚጣል ታሪፍን ተፈፃሚ አድርገዋል። በካናዳ ምርቶች ላይ የተጣለው የንግድ ቀረጥ ወደ 35 በመቶ ከፍ ማለቱ ቀድሞውንም የተወጠረው የንግድ ግንኙነት ይበልጥ…