02
Jul
ለኢትዮጵያ ተጨማሪ ከ460 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር ያፀደቀው የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ከአዳዲስ የብድር ጫና እንድትቆጠብ አስጠንቅቋል፡፡ ኢትዮጵያ ከእዳ ጫና እንድትላቀቅ በምትፈጽማቸው አዳዲስ የብድር ስምምነቶች ዙሪያ የጥንቃቄ እርምጃዎችን ልትወስድ እንደሚገባ አስታውቋል። ተቋሙ አምስተኛውን የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ግምገማ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ተጨማሪ 464 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለኢትዮጵያ አጽድቋል። የተቋሙ የበጀት ድጋፍ ከሁለት አመት በፊት ያፀደቀውና ለአራት አመት በሂደት የሚለቀቅ በሚል የፈቀደው የ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ብድር አካል ነው፡፡ የአይኤምኤፍ የስራ አመራር ቦርድ ያፀደቀው የ464 ሚሊዮን ዶላር ብድር እስካሁን በአራት ዙር ከተለቀቀው ሁሉ የላቀ ሲሆን ለወደፊቱ ከሚለቀቀው ብድር ታሳቢ የሚደረግ የ200 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ገንዘብ ታክሎበታል። ጭማሪ ገንዘቡ…