03
Mar
በክቡር ገና በሀገራችን “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የሚል ምሳሊያዊ አነጋገር አለ፡፡ አጋም እሾሀማ ተክል ሲሆን ቁልቋል ደግሞ ለመወጋት የተመቸ ጠፍጣፋ ቅጠል መሰል አካል ያለው ተክል ነው፡፡ አጋሙ በጠንካራ እሾሁ ቁልቋሉን ሲወጋው ልክ ህመሙ ያሰቃየው ይመስል ከጠፍጣፋ አካሉ እንደ እንባ ነጭ ፈሳሽ ያነባል፡፡ እናም “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል” የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ እንደሚኖር ሁሉ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የተጠጋም ሀገር ያለጥርጥር ሲያለቅስ ይኖራል፡፡ ከአይ ኤም ኤፍ ተጠግተው ሲያለቅሱ የኖሩ በርካታ ሀገራትን መጥቀስ ቢቻልም አርጀንቲና፣ ግብጽ፣ ናይጄሪያና ዛምቢያ ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ ተራው የኢትዮጵያ ነው፡፡ በቅርቡም የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂዎሪጄቫ ኢትዮጵያን ጎብኝተው “ በአዲስ…