China

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በሀገሪቱ እያጋጠመን ይገኛል ባሉት ተግዳሮቶች ወደ ጎረቤት ሀገራት እየሄዱ መሆኑን ገለፁ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ቀዳሚ የሆኑት የቻይና ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሌሎች ሀገራት እየተሰደዱ መሆኑን ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑት የቻይና ባለሃብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጋጠማቸው በመንግስት አመቺ የስራ ሁኔታዎች እየተሰጠ ባለመሆኑ ወደ ጎሮቤት ሃገራት ማለትም ወደ ኬንያ ፣ ኡጋንዳ እንዲሁም ታንዛኒያ እያማተሩ እንደሚገኙ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት በብዙ ምክንያቶች ቻይናውያን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን ንግዳቸውን ወደ ጎሮቤት አገሮች አዙረዋል ። "ይህ ለኤምባሲው ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ስጋት ነዉ ምክንያቱም የእኛ ተልዕኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለዉን ትብብር…
Read More
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

የተትረፈረፈ የነዳጅ ሀብት ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ደቡብ ሱዳን ከዚህ በፊት ነዳጇን በሱዳን በኩል አድርጋ ለዓለም ገበያ ስታቀርብ ቆይታለች፡፡ ሱዳን በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መሆኗን ተከትሎ እስከ ፖርት ሱዳን የተዘረጋው የደቡብ ሱዳን ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር በጦርነቱ ወድሞባታል፡፡ በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተገልጿል፡፡ በቻይና አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የሚዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከቻይና ብሔራዊ ነዳጅ ኮርፖሬሽን ሃላፊ ዳይ ሁሊያንግ ጋር በቤጂንግ መምከራቸውን የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ የቻይናው ነዳጅ ኮርፖሬሽን…
Read More
የፓሪስ ክለብ እና ቻይና ኢትዮጵያ አዲስ ብድር እንድታገኝ ፈቀዱ

የፓሪስ ክለብ እና ቻይና ኢትዮጵያ አዲስ ብድር እንድታገኝ ፈቀዱ

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ሊሰጠው ያሰበውን ብድር እና እርዳታ የከለከለው፡፡ ጦርነቱ እንዲቆም ያደረገው የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት የቆመውን ጨምሮ አዲስ ብድር እንዲሰጣት ለተቋሙ ጥያቄ ያቀረበች ቢሆንም በተደጋጋሚ የተደረጉ ውይይቶች የታሰበውን ያህል ፍሬ ሳያፈሩ ቆይተዋል፡፡ አይኤምኤፍ በድር ለኢትዮጵያ ከመፍቀዱ በፊት 20 አባላት ያሉት ፓሪስ ክለብ በመባል የሚጠራው የበለጸጉ ሀገራት ስብስብ ብድር እንዲሰጥ ይሁንታ እንዲሰጥ ሲጠበቅ ነበር፡፡ የሀገራትን ብድር የመክፈል አቅም በመገምገም ውሳኔ የሚሰጠው ይህ ስብስብ የኢትዮጵያንም አቅም ሲገመግም ቆይቶ ለአይኤምኤፍ ፈቃድ እንደሰጠ ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡ ከፓሪስ ክለብ በተጨማሪም ሌላኛዋ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ብድር የሰጠችው ቻይና ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ ተጨማሪ ብድር እንዲሰጣት ይሁንታቸውንን ሰጥተዋልም…
Read More
ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች አስመረቀች

ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች አስመረቀች

ቻይና በአማርኛ ቋንቋ ያስተማረቻቻውን የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን በትናትናው እለት አስመርቃለች። በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) በትናንትናው ዕለት ተማሪዎቹን ያስመረቀ ሲሆን፤ ከተመራቂዎቹ መካከልም በአማርኛ ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ ያስተማራቸውን ተማሪዎቹ ይገኙበታል። በቻይና የኢትዮጵያ ኤማባሲ ተወካዮች ቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) የአማርኛ ቋንቋ ተማሪዎች ምርቃት ላይ መሳተፋቸውንም ኤምባሲው አስታውቋል። “በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU በቻይና ውስጥ ብቸኛው የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍል የሚሰጥ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን፤ ትናንት ከተመረቁት መካከል የመጀመሪያው ዙር የአማርኛ ተማሪዎች ይገኙበታል ብሏል ኤምባሲው ባወጣው መረጃ። ኤምባሲው ቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት መስጠቱን አመስግኖ፤ “ይህ የሁለቱን ሀገራት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ያጠናክራል” ብሏል። የቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲ ለቻይናውያን ተማሪዎች የተዘጋጁ የአማርኛ መማሪያ…
Read More
ቻይና በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተስማማች

ቻይና በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተስማማች

ይህ የቴክኖሎጂ ልህቀት ማዕከል ግንባታ ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ይፈጃል ተብሏል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና የቻይናው ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የቴክኖሎጂ ልኅቀት ማዕከል ለመገንባት የውል ስምምነት ሠነድ ተፈራርመዋል፡፡ የልህቀት ማዕከል ግንባታው ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ግቢ ውስጥ ይገነባል የተባለ ሲሆን ለፕሮጀክቱ 9 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ተመድቧል ተብሏል፡፡ ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሽፈራው ተሊላና የቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ኤክስኪዩቲቭ ማኔጅንግ ዳይሬክተር ው ጁይ ናቸው፡፡ ማዕከሉ ሲጠናቀቅ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር የተጣጣመና ለደንበኞች የሚሰጠውን አገልግሎት አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ የሚያደርግ እንደሆነ አቶ ሽፈራው ገልጸዋል፡፡ ው ጁይን  በበኩላቸው የማዕከሉን ግንባታ በተያዘለት ጊዜ በጥራት  አጠናቅቀው እንደሚያስረክቡ አረጋግጠዋል፡፡ ማዕከሉ የኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ ሙያ የሰው ኃይል…
Read More
የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

የብሪክስ መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ መካሄድ ጀመረ

ከ15 ዓመት በፊት በብራዚል፣ ሩሲያ፣ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው ብሪክስ የዘንድሮውን ጉባኤ በጆሀንስበርግ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ፒንግ፣ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተገኝተዋል፡፡ ሩሲያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሰርጊ ላቭሮቭ የተወከለች ሲሆን ፕሬዝዳንት ፑቲን በበይነ መረብ ታግዘው ንግግር አድርገዋል፡፡ የጉባአው አዘጋጅ ደቡብ አፍሪካ ለ60 ሀገራት ግብዣ ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ40 በላይ የዓለማችን ሀገራት የብሪክስ አባል ለመሆን ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ሳውዲ አረቢያ፣ ኢራን፣ የተባበሩት አረብ አምሬት፣ ግብጽ፣ አልጀሪያ እና ሌሎችም ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል በይፋ…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ኢትዮጵያ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላከ የአህያ ስጋ 300 ሺህ ዶላር ማግኘቷን ገለጸች

ቻይና ዋነኛዋ የኢትዮጵያ አህያ ስጋ የተላከባት ሀገር ስትሆን ፍላጎቱ እያደገ እንደሆነም ተገልጿል። በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ሆንግኮንግ በመላክ 3 መቶ ሺህ ዶላር ገቢ ማግኘቷን የእንስሳት ልማት ኢንስትቲዩት አስታውቋል፡፡ በኢንስትቲዩቱ ምክትል ዋና  ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ሳህሉ ሙሉ እንደተናገሩት፣ ከአህያ ስጋ ውጪ የአህያ ቆዳን እንደ ቻይና ያሉ ሃገራት ለመድሃኒትነት በስፋት ሲጠቀሙበት የሚስተዋል በመሆኑ የስጋ ምርቱን ወደ ሆንግኮንግ እንዲላክ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ገቢው  የተገኘውም በተጠናቀቀው በጀት አመት 140 ቶን የአህያ ስጋ ምርትን ወደ ውጪ ገበያ በመላክ እንደሆነ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ በበጀት አመቱ 600 ቶን የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ለመላክ አስቀድሞ ታቅዶ እንደነበር ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡ በአህያ ስጋ የወጪ ንግድ  ዙሪያ የቄራ ድርጅቶች…
Read More
ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ዋና መቀመጫውን ቻይና ያደረገው ቴክኖ ሞባይል አዲስ የሞባይል ምርቱን ለኢትዮጵያ ደንበኞቹ በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል። ቴክኖ ሞባይል ይፋ ያደረገው ካሞን 20 አዲስ ምርት የአምስተኛ ትውልድ ወይም 5G ኔትወርክ አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል። እንዲሁም ይህ አዲስ ስልክ 8 ጌጋ ባይት ራም እና 256 ጌጋ ባይት መጠን ያላቸው መረጃዎችን የመያዝ አቅም ሲኖረው ለተክም ሰዓት ማስጠቀም የሚያስችል ባትሪም አለው ተብሏል። ሶስት ካሜራ እንዳለው የተገለጸው ይህ አዲስ የቴክኖ ሞባይል ስልክ ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ ለደንበኞቹ ቀርቧል። ቴክኖ ሞባይል በትራንሽን ኩባንያ ስር ሆኖ በፈረንጆቹ 2006 ላይ የተመሰረተ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው። በጆርጁ ዙ የተቋቋመው ቴክኖ ሞባይል ዋና መቀመጫውን በቻይናዋ ሸንዘን አድርጎ በመላው ዓለም ምርቶቹን ለደንበኞቹ በማቅረብ…
Read More
በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ሁዋዌ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ባካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተወዳደሩት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች የተሳተፉ  ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎች  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ ሴኪዩሪቲ፣ WLAN፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ AI፣ OpenEuler እና OpenGaussን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ  ተሳትፈዋል። በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች የራሳቸውን የፈጠራ ሃሳብ ይዘው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎቹ “የግእዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ መወዳደሪያ ይዘው ቀርበዋል፡፡ የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ…
Read More
ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ

ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ

ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ የዓለማችን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ እና ብዙ ህዝብ ያላቸው ሩሲያ እና ቻይና የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ የሆነው አማርኛ ቋንቋ ለዜጎቻቸው እንዲሰጥ መወሰናቸውን አስታውቀዋል፡፡ ሩሲያ ከቀጣዩ መስከረም ወር ጀምሮ በሞስኮ በሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጻለች፡፡ ትምህርቱ ከቀጣዩ መስከረም 2016 ዓ.ም ጀምሮ ይሰጣል የተባለ ሲሆን በሳምንት ሁለት ክፍለ ጊዜ እንደሚሰጥ በሞስኮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የእስያ እና አፍሪካ ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አሌክሲ ማስሎቭ ገልጸዋል፡፡ ሌላኛዋ አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቿ ለማስተማር የወሰነችው ሀገር ቻይና ስትሆን ትምህርቱ በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) ከሚሰጡ 101 የውጭ ቋንቋ ትምህርቶች አንዱ ይሆናል ተብሏል፡፡ ለዚህ እንዲረዳም አማርኛን ለቻይናዊያን ተማሪዎች ለማስተማር የሚያግዘው መጽሀፍ በቤጂንግ…
Read More