22
Jan
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባው በቻይና እስር ቤት ለረጅም ጊዜ በሞት ፍርድ ጥላ ስር የምትገኘውን ኢትዮጵያዊቷን ናዝራዊት አበራን ወደ ሀገሯ ለመመለስ መፍትሔ ይሰጣል የተባለለትን የፍርደኞች ማስተላለፍ ስምምነት አዋጅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ይህንን ስምምነት ያጸደቀው ከቻይና በተጨማሪ ከብራዚል ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ጋር የተደረገውን የፍርደኞች ማስተላለፍ እና ከደቡብ አፍሪካ ጋር የተፈረመውን በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነቶችን ጨምሮ ነው። በውይይቱ ወቅት በተለይም ከቻይና ጋር የተደረገው ስምምነት ለዓመታት በፍርድ ሂደት ላይ የምትገኘውን ናዝራዊት አበራን ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ የሕግ ማዕቀፍ እንደሚሆን ተገልጿል። ይሁን እንጂ በዕለቱ የምክር ቤት አባላት በስምምነቱ ላይ የተለያዩ አመለካከቶችን ያነሱ ሲሆን የሁለቱ ወገኖች የክርክር ነጥብም የአዋጁን አስፈላጊነትና የሉዓላዊነት…