Brazil

ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ ተስማማች

ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ ተስማማች

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባው በቻይና እስር ቤት ለረጅም ጊዜ በሞት ፍርድ ጥላ ስር የምትገኘውን ኢትዮጵያዊቷን ናዝራዊት አበራን ወደ ሀገሯ ለመመለስ መፍትሔ ይሰጣል የተባለለትን የፍርደኞች ማስተላለፍ ስምምነት አዋጅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ይህንን ስምምነት ያጸደቀው ከቻይና በተጨማሪ ከብራዚል ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ጋር የተደረገውን የፍርደኞች ማስተላለፍ እና ከደቡብ አፍሪካ ጋር የተፈረመውን በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነቶችን ጨምሮ ነው። በውይይቱ ወቅት በተለይም ከቻይና ጋር የተደረገው ስምምነት ለዓመታት በፍርድ ሂደት ላይ የምትገኘውን ናዝራዊት አበራን ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ የሕግ ማዕቀፍ እንደሚሆን ተገልጿል። ይሁን እንጂ በዕለቱ የምክር ቤት አባላት በስምምነቱ ላይ የተለያዩ አመለካከቶችን ያነሱ ሲሆን የሁለቱ ወገኖች የክርክር ነጥብም የአዋጁን አስፈላጊነትና የሉዓላዊነት…
Read More
የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው።

የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ኢትዮጵያን ሊጎበኙ ነው።

የደቡብ አሜሪካዋ ብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ አፍሪካ እንደሚመጡ ተገልጻል። እንደ ብራዚል ዜና አገልግሎት ዘገባ ከሆነ ፕሬዝዳንት ዳ ሲልቫ የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ አዲስ አዲስ አበባ ይመጣሉ። ፕሬዝዳንት ዳ ሲልቫ በአዲስ አበባ ቆይታቸው በ37ኛው የአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባኤ ላይ እንደሚሳተፉም ተገልጿል። ፕሬዝዳንት ዳ ሲልቫ ከአዲስ አበባ በተጨማሪም በግብጽ ጉብኝት እንደሚያደርጉም ተገልጿል። ከአፍሪካ በመቀጠል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጥቁር ህዝቦች የሚኖሩባት ብራዚል ከአፍሪካ ጋር የሚያስተሳስራት ብዙ ታሪክ አላት። ፕሬዝዳንቱ ዳ ሲልቫ ስለ ጉብኝታቸው እንዳሉት "ብራዚል ከአፍሪካ ጋር ያለባትን የታሪክ እዳ መክፈል ትፈልጋለች" ብለዋል። ለሁለተኛ ጊዜ ወደ አፍሪካ የሚጓዙት ፕሬዝዳንት ሲልቫ ከዚህ በፊት በአንጎላ፣ ኬፕ ቩርዴ እንዲሁም በሳኦቶሜ…
Read More