Chinaembassyinethiopia

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በሀገሪቱ እያጋጠመን ይገኛል ባሉት ተግዳሮቶች ወደ ጎረቤት ሀገራት እየሄዱ መሆኑን ገለፁ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ቀዳሚ የሆኑት የቻይና ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሌሎች ሀገራት እየተሰደዱ መሆኑን ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑት የቻይና ባለሃብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጋጠማቸው በመንግስት አመቺ የስራ ሁኔታዎች እየተሰጠ ባለመሆኑ ወደ ጎሮቤት ሃገራት ማለትም ወደ ኬንያ ፣ ኡጋንዳ እንዲሁም ታንዛኒያ እያማተሩ እንደሚገኙ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት በብዙ ምክንያቶች ቻይናውያን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን ንግዳቸውን ወደ ጎሮቤት አገሮች አዙረዋል ። "ይህ ለኤምባሲው ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ስጋት ነዉ ምክንያቱም የእኛ ተልዕኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለዉን ትብብር…
Read More
ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

በቻይና በሲሚንቶ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ ሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገልጿል። በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው የሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ሊቀመንበር እና የሲኤንቢኤም ተቋም ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ሚስተር ሉ ያን እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ተወያይተዋል። ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስት በሚደረግበት ዙሪያ ቤጂንግ በሚገኘው የኩባንያው ዋና ጽ/ቤት ተገኝተው ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ተፈራ በውይይቱ ወቅት ኩባንያው በኢትዮጵያ ባሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከዲዛይን ጀምሮ በግንባታ ረገድ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ በኢትዮጵያ ካለው የግንባታ ስፋት አንጻር የሲሚንቶ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። አምባሳደር ተፈራ አያይዘውም፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ ፍላጎት ግምት ውስጥ በማስገባት በኢንቨስትመንቱ ዘርፍ ቢሰማራ የጋራ ተጠቃሚነቱ ሰፊ መሆኑን ገልጸዋል።…
Read More