fdiethiopia

ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

ኢትዮጵያ 10 የኢንዱስትሪ ፓርኮቿን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንነት አሳደገች

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስፈላጊዉን መስፈርት አሟልተዋል ያላቸዉን 10 ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን እንዲያድጉ መወሰኑ ተገልጿል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በበኩሉ እንዳስታወቀው በስሩ ከሚያስተዳድራቸው 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮችና የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና መካከል 10ሩ ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ማደጋቸውን አሳዉቋል። አሁን በስራ ላይ ካሉ 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮች መካከል ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ያደጉት አዳማ ባህርዳር ፣ ቦሌ ለሚ ፣ ደብረ ብረሃን እና ሀዋሳ ፣ ጅማ ፣ ቂሊንጦ ፣ ኮምቦልቻ ፣ መቀሌ እና ሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መሆናቸው ታዉቋል። በኢትዮጵያ የሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለማሳደግ አዋጅ ቁጥር 1322/2016 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል። ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ…
Read More
የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ ጎረቤት ሀገራት እየተሰደዱ ነው ተባለ

በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታ የቻይና ባለሃብቶች በሀገሪቱ እያጋጠመን ይገኛል ባሉት ተግዳሮቶች ወደ ጎረቤት ሀገራት እየሄዱ መሆኑን ገለፁ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ላይ ቀዳሚ የሆኑት የቻይና ባለሀብቶች እና ኩባንያዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ ሌሎች ሀገራት እየተሰደዱ መሆኑን ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ዋነኛ ተዋናይ የሆኑት የቻይና ባለሃብቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያጋጠማቸው በመንግስት አመቺ የስራ ሁኔታዎች እየተሰጠ ባለመሆኑ ወደ ጎሮቤት ሃገራት ማለትም ወደ ኬንያ ፣ ኡጋንዳ እንዲሁም ታንዛኒያ እያማተሩ እንደሚገኙ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ተወካይ እንደተናገሩት በብዙ ምክንያቶች ቻይናውያን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ያላቸውን ንግዳቸውን ወደ ጎሮቤት አገሮች አዙረዋል ። "ይህ ለኤምባሲው ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ስጋት ነዉ ምክንያቱም የእኛ ተልዕኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለዉን ትብብር…
Read More
ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

ኢትዮጵያ የሲንጋፖር ኩባንያን ወደ ሀገሯ እንዲመጣ ጋበዘች

የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጥሪ ቀረበ ዓለም አቀፍ የእስያ ኩባንያዎችን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እና ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማሳመን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሲንጋፖርን በመጎብኘት ላይ ናቸው፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ ጋር በመሆን ሲንጋፖር የሚገኘውን የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን ጎብኝተዋል። ሁለቱ የኢንቨስትመንት አመራሮች ከሲንጋፖር ወደብ ባለስልጣን ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይቱም የሲንጋፖር የወደብ ባለስልጣን በኢትዮጵያ በሎጀስቲክስ ኢንቨስትመንት እንዲሰማራ ጠይቀዋል። የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ከፍተኛ ፍላጎት ገልፀው ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት የሚሰማራበትንና ልምድ የሚያካፍልበት መንገድ እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ በበኩላቸው ፈጣን…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰት የሁለት ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅዳ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረበው ሪፖርቱ ላይ እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት 2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር አግኝታለች፡፡ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ እንዳሉት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ወደ አገር ውስጥ ለመሳብ ታቅዶ 2.67 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡ የኮሚሽኑ አፈጻጸም የዕቅዱን 61 በመቶ ብቻ ያሳካ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት፣ በኦሮሚያ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያለው አለመረጋጋት እንዲሁም በዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ምክንያት ያጋጠመው የዓለም ኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ለአፈጻጸሙ መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው ተብሏል፡፡ ወደ…
Read More
ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

ከኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 51 ባለሀብቶች ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኢንቨስተሮች በሙስና ምክንያት ከሚሰሩባቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለቀው እየወጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የበጀት ዓመቱን ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ የምርት ዘርፎች የተሰማሩ የውጭ ሀገራት ኩባንያዎች ከመንግስት ተቋማት መሪዎች እና ባለሙያዎች በሚጠየቁ ክፍያ ምክንያት መማረራቸው ተገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ የኢንቨስትመንት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በገመገመበት ወቅት እንደገለጸው በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ኢስተርን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያሉ ኩባንያዎች ቅሬታ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት በዚህ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባደረጉት ምልከታ ኢንቨስተሮች የሚጠይቋቸውን ከትንሽ እስከ ትልቅ አገልግሎቶች በገንዘብ እየገዙ ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም በፓርኩ ላይ የባለቤትነት ስሜት ባለመኖሩ ፓርኮች ውስጥ እየገቡ ዘረፋ እየተፈጸባቸው መሆኑን የምክር…
Read More
ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

የከፊ ሚኒራልስ ኩባንያ አካል የሆነው ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ 'PW ማይኒንግ' ጋር የወርቅ ማዕድን ልማትና በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የተፈረመው ከትናንት ሚያዚያ 18/2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ በሚገኘው፤ “ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2023” ዓለም አቀፍ የንግድ ተቋማትና ባለሃብቶች ፎረም ጎን ለጎን ነው። በፎረሙ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ባለሃብቶች፣ የንግድ ተዋንያን፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ሥራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ሲሆን፤ በመድረኩ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የተመረጡ ኩባንያዎች ጉብኝትና አውደ ርዕይዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚከናወነው ይህ ፎረም በግብርና፣ ማንፋክቸሪንግ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ ማዕድን እና በቱሪዝም ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨሰትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ፣…
Read More