Export

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ማደጉ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ መጠባበቂያ ከሶስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ማደጉ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከባንኮች የውጭ ንግድ ግብይት ብቻ በየወሩ 500 ሚሊዮን ዶላር እያገኘች እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ካሳለፍነው ሐምሌ ወር ጀምሮ የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያ እንዲመራ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምኅረቱ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ በሰጡት መግለጫ የባንኮች የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከወጪ ንግድ ብቻ በወር በአማካይ 500 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል ብለዋል፡፡ ዋና ገዢው አክለውም የባንክ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረበት 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ወደ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ማደጉንም ገልጸዋል፡፡ አቶ ማሞ አክለውም ከኹለት ሳምንት በፊት በባንኮች መካከል በተጀመረው የእርስ በርስ የውጭ ምንዛሬ ግብይት ከ100 ሚሊዮን ዶላር በላይ ግብይት እንደተካሄደም ተናግረዋል። የተለያዩ ምርቶችን ወደ ውጭ ሀገራት…
Read More
ኢትዮጵያ የአትክልት ምርቶችን ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ ገበያ አቀረበች

ኢትዮጵያ የአትክልት ምርቶችን ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ ገበያ አቀረበች

በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የአትክልት ምርቶች በመርከብ ለአውሮፓ ገበያ ተልከዋል፡፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የአትክልት ምርቶች በመርከብ ተጓጉዘው ለአውሮፓ ገበያ መላካቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ኢትዮ ቬጅ ፍሩ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በተሰኘ የአትክልትና ፍራፍሬ አምራች ድርጅት በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሹገር ስናብ እና ማንጄቱት የተባሉ የአትክልት ምርቶችን በመርከብ በማጓጓዝ ወደ ኔዘርላንድ መላኩ ተጠቅሷል። በዚህም 12 ቶን ሹገር ስናብ እና ማንጄቱት የአትክልት ምርቶችን ዘመናዊ የማቀዝቀዣ እና አዳዲስ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ኮንቴነር በመጠቀም ጅቡቲ ወደብ ከደረሰ በኃላ በመርከብ መላኩ ተገልጿል። የአትክልት ምርቱ ከቆቃ ተነስቶ በመርከብ ተጓጉዞ በ23 ቀናት ውስጥ ኔዘርላድ እንደሚደርስም ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የአውሮፓ ሀገራት የኢትዮጵያ ግብርና ምርቶች ዋነኛ መዳረሻ ሲሆን ከጠቅላላው…
Read More
ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች 

ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች 

በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሦስት ወራት ከወጪ ንግድ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ገልጸዋል። ሚኒስትሩ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) አፈጻጸምን ከላኪዎች ጋር መገምገማቸውን አስታውቀዋል። አፈጻጸሙ በምርት ጭማሪም ሆነ በውጭ ምንዛሪ ዕድገት ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ለውጥ ማሳየቱን አመላክተዋል። ይህም ከዕቅዱ 132 በመቶ መሳካቱንና ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንጻር ከ700 ሚሊየን ዶላር በላይ ጭማሪ አለው ተብሏል። በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን በማላቅ ኢኮኖሚው የሚፈልገውን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ ከዘርፉ ተዋናዮች እና ከላኪዎች ጋር የጋራ መግባባት ላይ መደረሱንም አመላክተዋል። ይህ በዚህ…
Read More
የኢትዮጵያ ውጪ ንግድ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ ውጪ ንግድ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ጉድለት አሳየ

ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት ወደ ውጭ ከሚላኩ ምርቶች 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዳ ነበር፡፡ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስታውቋል፡፡ የተገኘው ገቢ ባለፈው በጀት ዓመት ከተገኘው 3 ነጥብ 64 ቢሊየን ዶላር የ4.6 በመቶ ወይም በ166 ሚሊዮን ዶላር ብልጫ አለው፡፡ ከተገኘው ገቢ የግብርናው ዘርፍ 76 በመቶ በመያዝ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘ ሲሆን ማኑፋክቸሪንግ ማእድን ፣ኤሌክትሪክና ሌሎች በተከታታይ የሚገኙ ናቸው። ኢትዮጵያ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከ3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን በላይ ነዳጅ ከውጭ ሀገራት ግዢ በመፈጸም ለተጠቃሚዎች እንደተሰራጨም ተገልጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ኢትዮጵያ 4 ቢሊዮን…
Read More
ኢትዮጵያ በየዓመቱ 100 ሺህ ሔክታር መሬት በአዲስ የቡና ዝርያ እየተካች መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በየዓመቱ 100 ሺህ ሔክታር መሬት በአዲስ የቡና ዝርያ እየተካች መሆኗ ተገለጸ

የሀውቲ ታጣቂዎች በቀይ ባህር ላይ ባደረሱት ጥቃት የኢትዮጵያ ቡና ንግድ ለሶስት ቀናት ተስተጓጉሎ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በ2016 በጀት ዓመት የውጪ ንግድ አፈጻጸም ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንዳሉት ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት ውስጥ 350 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር ብለዋል፡፡ ይሁንና አፈጻጸሙ 298 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አውሮፓ ሀገራት የምትልከው ቡና በቀይ ባህር በኩል በመሆኑ እና የሀውቲ ታጣቂዎች በሚያደርሱት ጥቃት ምክንያት መስጓጎል ገጥሞት እንደነበርም ተገልጿል፡፡ እንደ ዋና…
Read More
ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአበባ ንግድ ከ300 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት ከአበባ ኤክስፓርት ከ 3 መቶ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች፡፡ የሆርቲካልቸር ኢንቨስትመንት ዘርፍ በተለይም የአበባ ኤክስፖርት ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከፍተኛ አስተዋጽኦን  እያበረከተ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል። በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንት እና ምርት ግብይት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ አበበ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፋት አስር ወራት 79 ሺህ 819 ቶን የአበባ ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 392 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ አግኝታለች ብለዋል። የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአብዛኛው ወደ አውሮፓና ኤዥያ ሀገራት እንደሚላክ  የተናገሩት   ስራ አስፈፃሚው  ምርጥ አስር ተብለው ከተለዩት ተቀባይ ሀገራት መካከል ደግሞ ኔዘርላንድ ትልቁን ድርሻ ትይዛለች ብለዋል።  በበጀት አመቱ አስር ወራት ከእቅድ አፈፃፀም አንጻር ሲታይ የተገኘው ገቢ…
Read More
ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ ፈቀደች

ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርቡ ፈቀደች

ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን እና የውጪ ንግድን ለማሳደግ በሚል ነበር ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የገነባችው፡፡ አሁን ላይ 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሏት ኢትዮጵያ ፓርኮች የምርታቸውን 50 በመቶ ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ ፈቅዳለች፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች 50 በመቶ ምርታቸውን ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ መፈቀዱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል። በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች ምርታቸውን ሙሉ በሙሉ ለውጭ ገበያ እንጂ ለሀገር ውስጥ ማቅረብ ሳይፈቀድላቸው መቆየቱን የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን ገልጸዋል። ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ተጽዕኖ ሥር የነበሩ ባለሃብቶችን ለማበረታታት በፓርኮች ውስጥ የሚሰሩ ኩባንያዎች 50 በመቶ ምርታቸውን ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡ በአዋጅ መፈቀዱን አስታውቀዋል። ከሁለት ዓመት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ አሜሪካ…
Read More
ብሪታንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ አምስት የአፍሪካ ሀገራት አበባ ያለ ግብር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

ብሪታንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ አምስት የአፍሪካ ሀገራት አበባ ያለ ግብር ወደ ሀገሯ እንዲገባ ፈቀደች

የብሪታንያ ንግድ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ብሪታንያ የአበባ ምርቶችን ወደ ሀገራቸው በሚያስገቡ ነጋዴዎች ላይ ጥላው የነበረውን ግብር አንስታለች፡፡ ሀገሪቱ ከዚህ በፊት የአበባ ምርቶች ወደ ብሪታንያ ሲገቡ 8 በመቶ ግብር መክፈል የነበረባቸው ሲሆን ከዛሬ ሚያዚያ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ማንሰቷን አስታውቃለች፡፡ የብሪታንያ ንግድ ኮሚሽነር ጆን ሀምፍሬይ እንዳሉት ወደ ብሪታንያ የሚገቡ የአበባ ምርቶች ከግብር ነጻ መሆናቸው የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አበባ አምራች እና ነጋዴዎችን ተጠቃሚ ከማድረጉ ባለፈ በብሪታንያ የአበባ ምርት በቅ አቅርቦት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ፣ኬንያ፣ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል አበባ ላኪ ሀገራት ናቸው፡፡ እነዚህ አምስት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት በቀጥታም ይሁን በሶተኛ ሀገር አድርገው ወደ ብሪታንያ ለሚያስገቡት የአበባ ምርት የገቢ…
Read More
ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

ኢትዮጵያ ከማዕድን ንግድ ከ252 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘሁ አለች

በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት ስምንት ወራት ከማዕድን ዘርፍ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል። የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ በ2016 በጀት ዓመት የተለያዩ ዓይነት ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ በመላክ 252 ነጥብ 15 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል። ባለፉት ስምንት ወራት ከሁለት ሺህ 673 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ፣ 66 ቶን በላይ ታንታለም እና ከ11 ሺህ 176 ቶን በላይ ሉቲየም ኦር ለውጭ ገበያ መቅረባቸውን ዘርዝረዋል። በተጨማሪም ከ99 ሺህ 021 በላይ ቶን የጌጣጌጥ እንዲሁም 29 ሺህ 281 ቶን በላይ የኢንዱስትሪ ማዕድናት ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ መቻሉን አቶ ሚሊዮን ተናግረዋል። የተገኘው ገቢ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት…
Read More
ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

በ2016 በጀት ዓመት ሥድስት ወራት 100 ሚሊየን ዶላር ማጣቱን የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር አስታውቋል። የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፀሐፊ እንዳለ ሰይፉ፥ ባለፉት ሥድስት ወራት 124 ሚሊየን ዶላር ከቆዳ ምርቶች ሽያጭ ለማግኘት ታቅዶ መሰራቱን ተናግረዋል። ይሁን እንጅ ማሳካት የተቻለው 14 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር ብቻ መሆኑን ተናግረው በግማሽ ዓመቱ የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል። የቆዳ ዘርፉ ከ2010 ዓ.ም በኋላ ባሉት ተከታታይ ዓመታት ከፍተኛ የገቢ ማሽቆልቆል እንዳጋጠመውም አስረድተዋል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሥራ ማስኬጃ በጀት እጦትና ለዘርፉ የተሰጠው የትኩረት ማነስ ለገቢው መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያትም የቆዳ ፋብሪካዎች ከሥራ…
Read More