Coffeeexport

ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ባለፉት አራት ወራት ከወጪ ንግድ ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ በተጠቀሱት ጊዜያት ውስጥ 480 ሺህ ቶን የተለያዩ ምርቶችን ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደተገኘ ተገልጿል፡፡ የተገኘው ገቢ ካምናው ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር የ947 ሚሊየን ዶላር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል፡፡ ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ ግብርና 53 ነጥብ 25 በመቶ ድርሻ ሲይዝ ማዕድን 37 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ 5 ነጥብ 43 በመቶ እንዲሁም ኤሌክትሪክና ሌሎች 4 ነጥብ 33 በመቶ ድርሻ ይዘዋል፡፡ ወርቅ፣ ቡና፣ ኤሌክትሪክ እና የጥራጥሬ ምርቶች በገቢም ሆነ በመጠን ከዕቅዳችው በላይ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ምርቶች መሆናቸውን የሚስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ ከተላኩ ምርቶች መካከል 150 ሺህ ቶን…
Read More
ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር በታሪክ ከፍተኛ መጠን ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በሐምሌ ወር በታሪክ ከፍተኛ መጠን ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳ ተገለጸ

ኢትዮጵያ እስከ ዛሬ ድረስ በአንድ ወር ውስጥ ለሽያጭ ካቀረበችው ቡና በአዲሱ የ2017 በጀት አመት ሀምሌ ወር ከፍተኛ ገቢ ማግኘቷ ተሰምቷል፡፡ በ2017 በጀት አመት ሀምሌ ወር ከቡና ሽያጭ ከ180 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና የኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረ መድህን እንደተናገሩት  ይህ አፈጻጸም እስከዛሬ ድረስ  በሁሉም የሀምሌ ወራት  ከተገኘው ገቢ  ጋር ሲነጻጸር ሪከርድን የሰበረ ነው ብለዋል። በበጀት ዓመቱ ሀምሌ ወር ለውጪ ገበያ ከቀረበዉ 40 ሺህ 532 ቶን ቡና ከ180 ሚሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘት ተችሏል፡፡ በዚህም  እስከዛሬ ድረስ በአንድ ወር ውስጥ ለውጭ ገበያ  ቀርቦ ከተገኘው  ገቢ አኳያ ሲነጻጸር ሪከርድን  መስበር ችሏል፡፡ከእቅድ አንፃር …
Read More
ኢትዮጵያ በየዓመቱ 100 ሺህ ሔክታር መሬት በአዲስ የቡና ዝርያ እየተካች መሆኗ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በየዓመቱ 100 ሺህ ሔክታር መሬት በአዲስ የቡና ዝርያ እየተካች መሆኗ ተገለጸ

የሀውቲ ታጣቂዎች በቀይ ባህር ላይ ባደረሱት ጥቃት የኢትዮጵያ ቡና ንግድ ለሶስት ቀናት ተስተጓጉሎ እንደነበር ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በ2016 በጀት ዓመት የውጪ ንግድ አፈጻጸም ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ የቡና እና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) እንዳሉት ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት ውስጥ 350 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር ብለዋል፡፡ ይሁንና አፈጻጸሙ 298 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ ሀገራት በመላክ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደተገኘ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ አውሮፓ ሀገራት የምትልከው ቡና በቀይ ባህር በኩል በመሆኑ እና የሀውቲ ታጣቂዎች በሚያደርሱት ጥቃት ምክንያት መስጓጎል ገጥሞት እንደነበርም ተገልጿል፡፡ እንደ ዋና…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከቡና ንግድ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ የቡና ንግድ በታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገቢ ማግኘቷን አስታውቃለች፡፡ ኢትዮጵያ ከቡና ወጪ ንግድ በዘንድሮው በጀት አመት ከአንድ ነጥብ 4 ቢሊዮን  ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አዱኛ ደበላ እንደገለፁት ኢትዮጵያ በ2016 በጀት አመት ከቡና ሽያጭ በመጠንም ሆነ በገቢ ከፍተኛ የሆነ ውጤት አስመዝግባለች ብለዋል። ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት 298 ሺህ 500  ቶን ቡና ለውጪ ገበያ አቅርባ 1 ነጥብ 43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በመጠንም ሆነ በገቢ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት እንደሆነ ዋና ዳይሬክተሩ  ጨምረው ገልፀዋል። የተላከው የቡና መጠን በ20 በመቶ እንዲሁም በዋጋ ደረጃም…
Read More
ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቅባት እና ጥራጥሬ እህሎች 285 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቅባት እና ጥራጥሬ እህሎች 285 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አገኘች

ባለፉት ስድስት ወራት ከቅባትና ጥራጥሬ እህሎች የወጪ ንግድ 285 ነጥብ 53 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከቅባት እህሎች የወጪንግድ 109 ነጥብ 66ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን አፈጻጸሙም 109 በመቶ መሆኑን ሚኒሰቴሩ በስድስት ወራት አፈጻጸም ሪፖርቱ ገልጿል፡፡ ይህም ካምናው ተመሳሳይ ወቅት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ26 ሚሊየን ዶላር ብልጫ እንዳለው ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡ በስድስት ወራቱ በጥራጥሬ እህል የተገኘው ገቢ 176 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የ77 ሚሊየን ዶላር ብልጫ እንዳለው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ከቅባትና ጥራጥሬ እህሎች የወጪ ንግድ በድምሩ 285 ነጥብ 53 ሚሊየን የአሜሪካን…
Read More
አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

አዲሱ የአውሮፓ ህብረት ሕግ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ገበሬዎች ላይ የሕልውና አደጋ ደቅኗል ተባለ

የአውሮፓ ህብረት ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው አዲስ ህግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን የሚጎዱ ምርቶችን ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ገበያዎች እንዳይገቡ እና እንዳይሸጡ አደርጋለሁ ብሏል፡፡ የምድርን ሙቀት ለመከላከል እና የደን ምንጣሮን ለመከላከል ይረዳል በሚል የተዘጋጀው ይህ ህግ ከደን ምርቶች ጋር የተያያዙ ምርቶች በአውሮፓ የገበያ እድል እንዳያገኙ መከልከል እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ማበረታታት የህጉ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ ይህ ሕግ የጫካ ቡናዎችን ወደ አውሮፓ እና ሌሎች ዓለም ገበያ መዳረሻዎች የምትልከው ኢትዮጵያን እንደሚመለከት ስጋቶች ተነስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቡና ማህበር ጉዳዩ እንዳሳሰበው ገልጾ አዲሱ የአውሮፓ ህግ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ እንዲረዳ ካልተደረገ ሚሊዮኖች ወደ ድህነት ሊወርዱ ይችላሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ሁሴን አምቦ (ዶ/ር) ለአልዐይን እንዳሉት “በኢትዮጵያ ቡና…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት መጠን ከዓመት ዓመት ማሽቆልቆሉን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ገልጿል፡፡ የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ ኢትዮጵያ በ2014 ዓ. ም ለዓለም ገበያ ያቀረበችው የቡና መጠን 302 ሺሕ ቶን ነበር። በዘንድሮው ማለትም በ2015 ዓመት ግን 240 ሺሕ ቶን ብቻ ቡና ለዓለም ገበያ ማቅረቧን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር አስታውቋል። ወደ ውጪ ሀገራት የተላከው ቡና ከባለፈው ዓመት ለዓለም ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት ጋር ሲንጻጸር በ62 ሺሕ ቶን ቅናሽ አሳይቷል ተብላል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም፤ ኢትዮጵያ በዘንድሮው ዓመት ለዓለም ገበያ ካቀረበችው ቡና 1 ነጥብ 33 ቢሊዮን ዶላር…
Read More