Goldexport

ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከውጪ ንግድ ሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ባለፉት አራት ወራት ከወጪ ንግድ ከ2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል፡፡ በተጠቀሱት ጊዜያት ውስጥ 480 ሺህ ቶን የተለያዩ ምርቶችን ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ እንደተገኘ ተገልጿል፡፡ የተገኘው ገቢ ካምናው ተመሳሳይ ወራት ጋር ሲነጻጸር የ947 ሚሊየን ዶላር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል፡፡ ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ ግብርና 53 ነጥብ 25 በመቶ ድርሻ ሲይዝ ማዕድን 37 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ 5 ነጥብ 43 በመቶ እንዲሁም ኤሌክትሪክና ሌሎች 4 ነጥብ 33 በመቶ ድርሻ ይዘዋል፡፡ ወርቅ፣ ቡና፣ ኤሌክትሪክ እና የጥራጥሬ ምርቶች በገቢም ሆነ በመጠን ከዕቅዳችው በላይ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ምርቶች መሆናቸውን የሚስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡ ከተላኩ ምርቶች መካከል 150 ሺህ ቶን…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይትን ማስቆም እንዳልቻለች ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከወርቅ ማዕድን 363 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ያቀደች ቢሆንም የተገኘው ግን 67 በመቶው ብቻ ነው ተብሏል፡፡ ህገ ወጥ የወርቅ ግብይት ዋነኛው ችግር መሆኑን ተከትሎ በመከላከያ ኮማንድ ፖስትና በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጭምር ክትትል ቢደረግም ህገ ወጥ የወርቅ ንግድን ማስቆም እንዳልተቻለ ማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በማዕድናት ሕገ ወጥ ግብይት፣ ኮንትሮባንድና የፀጥታ ችግር ምክንያት በባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ ሦስት ቶን ብቻ እንደሆነ፣ ይህም ከዕቅዱ 50 በመቶ ብቻ መሆኑ ታውቋል፡፡ በመጋቢት ወር ብሔራዊ ባንክ የገባው ወርቅ 350 ኪሎ ግራም ሲሆን ይህም በ2014 መጋቢት ወር ከተገኘው 800 ኪሎ ግራም በእጅጉ ያነሰ ነው ተብሏል፡፡ በአገሪቱ ያሉ ወርቅ…
Read More