17
Mar
በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው እንደሆነ የተገለጸ የብረን ማዕድን በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ጊምቢ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ለማውጣት ስምምነት ተፈርሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና ቻይናዊያን በተቋቋሙ ኩባንያዎች መካከል የብረት ማዕድን ልማት ፕሮጀክት ዛሬ ተፈራርሟል፡፡ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ አለው የተባለው ይህ የ10 ዓመት የብረት ማዕድን ማውጣት ስምምነት የማዕድን ሚኒስቴር እና ዜድ ዋይ ቲቢ-ዲኤይኤም ስቲል ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ የግል ኩባንያ ጋር ስምምነት ፈጽሟል፡፡ የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ከስምምነቱ በኋላ እንደገለጹት ኢትዮጵያ የብረት ማዕድናት እንዳሏት ካወቀች ከ70 ዓመት በላይ ቢሆናትም “እስካሁን አንድም የብረት ማዕድን አለማውጣቷን” ተናግረዋል፡፡ “በወለጋ ጊምቢ ቢቂላል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ብረት እንዳለን የታወቀው በ1956 ነበር፣ ግን እንደምታውቁት እስካሁን አንድም ብረት ማዕድን…