mininginethiopia

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

የከፊ ሚኒራልስ ኩባንያ አካል የሆነው ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ 'PW ማይኒንግ' ጋር የወርቅ ማዕድን ልማትና በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የተፈረመው ከትናንት ሚያዚያ 18/2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ በሚገኘው፤ “ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2023” ዓለም አቀፍ የንግድ ተቋማትና ባለሃብቶች ፎረም ጎን ለጎን ነው። በፎረሙ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ባለሃብቶች፣ የንግድ ተዋንያን፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ሥራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ሲሆን፤ በመድረኩ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የተመረጡ ኩባንያዎች ጉብኝትና አውደ ርዕይዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚከናወነው ይህ ፎረም በግብርና፣ ማንፋክቸሪንግ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ ማዕድን እና በቱሪዝም ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨሰትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ኢትዮጵያ ለሁለት የወርቅ አውጪ ኩባንያዎች ፈቀድ ሰጠች

ለሁለት ሀገር በቀል ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ ምርት ፈቃድ ተሰጥቷል። የማዕድን ሚኒስቴር ለሁለት ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የደለል ወርቅ የማምረት ፈቃድ መስጠቱን ገልጿል። ፈቃድ የተሰጣቸው ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ እና ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ የተሰኙት ሀገር በቀል ኩባንያዎች ናቸው። "ቤአኤካ" ፈቃድ የተሰጠው በጋምቤላ ብሄራዊ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ማንግሽ ወረዳ ሲሆን ለፕሮጀክቱ ከ138 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ ተገልጿል፡፡ ይህ ኩባንያ በሚቀጥሉት 4 ዓመታት ውስጥ 911 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ያመርታል ተብሏል። ሌላኛው ፈቃድ የተሰጠው ተቋም "ኢልኔት ቴክኖሎጂ ግሩፕ" ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አሶሳ ዞን፣ አሶሳ እና ሁዱሉ ወረዳዎች እንደሆነ ተገልጿል። ይህ ኩባንያ ለፕሮጀክቱ ከ148 ሚሊየን ብር በላይ መመደቡ አስታውቋል፡፡ የፈቃዱ የአገልግሎት ዘመን…
Read More