03
May
ዋና መቀመጫውን ፐርዝ አውስትራሊያ ያደረገው ግዙፍ የማዕድን አሳሽ አስካሪ ሜታልስ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ውስጥ አዲስ የኢንቨስትመንት ውል ፈጽሟል። አስካሪ ሜታልስ የተባለ የማዕድን አሳሽ ኩባንያ በአፍሪካ ያለውን የፍለጋ እንቅስቃሴውን ወደ ኢትዮጵያ በማስፋፋት ሪፍት ቫሊ ሜታልስ የተባለውን የግል ኩባንያ ሙሉ በሙሉ ለመግዛት ስምምነት ላይ መድረሱን በይፋ አስታውቋል። ሪፍት ቫሊ ሜታልስ በደቡባዊ ኢትዮጵያ በሚገኘው በአዶላ አካባቢ አምስት ትላልቅ የወርቅ ፕሮጀክቶች ባለቤት ሲሆን፣ ይህ ስምምነት አስካሪ ሜታልስ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 350 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኙትን ሳካሮ፣ ሳካሮ ምዕራብ፣ ሌጋ ደምቢ ደቡብ፣ ሜጋዶ እና ዋዩ ቦዳ የተባሉትን 460 ካሬ ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ ፕሮጀክቶች እንዲያገኝ አስችሎታል። ይህ ስምምነት አስካሪ ሜታልስ ከፍተኛ መጠን ያለው የወርቅና የመዳብ…