EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ መብረር አቆመ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መግለጫ ከነገ ነሀሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያቆም አስታውቋል፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ አስመራ እና ከአስመራ ወደ አዲ አበባ የሚደረጉ በረራዎችን አቋርጫለሁ ያለው አየር መንገዱ በኤርትራ ያለው አሰራር አስቸጋሪ እና ከቁጥጥሩ ውጪ መሆኑ ለበረራው መቋረጥ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ ጉዞ ለማድረግ ቲኬት የገዙ መንገደኞችም በመረጡት አየር መንገዶች እንዲበሩ እንደሚያደርግ እና የዋጋ ጭማሪ እንደማያደርግም አየር መንገዱ ገልጿል፡፡ ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ከመስከረም 30 በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር መከልከሏ ይታወሳል፡፡ የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከአንድ ወር በፊት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ በሚጓዙ ተጋዦች ላይ “የተደራጀ እና ስልታዊ የሻንጣ ስርቆት፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ፣…
Read More
በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

በአዲስ አበባ ያለው ከባድ አየር ንብረት የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲስ አበባ በተከሰተው ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር ምንክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እያዘዋወረ መሆኑን አስታወቀ በአዲስ አበባ በተከሰተዉ ከፍተኛ ጭጋጋማ አየር አብዛኛው በረራዎች ቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ሊያርፍ ባለመቻሉ ምክንያት ወደ ሌላ አየር ማረፊያዎች እንዲቀየሩ መደረጉን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል ። አየር መንገዱ እንደገለፀው ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ባለዉ ከፍተኛ ጭጋግ ( ጉም) ምክንያት የአየር ማረፊያዎችን ወደ ሌላ ቦታ እያዘዋወረ መሆኑን እና ይህም በሀገር ዉስጥ እና በአለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተፅዕኖ አሳድሯል ብሏል። በተጓዦች ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ በተጓዦች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ መጉላላቶችን ለመቀነስ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ…
Read More
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሸለሙ

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክተዋል። የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የህይወት ዘመን ሽልማት አበርክታለች። ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ለአሜሪካዊያን አገልግሎት የሰጡ ተቋማትን እና ግለሰቦችን የህይወት ዘመን ሽልማት ይሰጣል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት 25 ዓመታት በአሜሪካ ለሚኖሩ ዜጎች በሰጠው አገልግሎት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኗል። አየር መንገዱ ሽልማቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ "ሽልማቱ ለሰጠው አገልግሎት እውቅና የሰጠ ነው" ብሏል። ፕሬዝዳንት ባይደን የፈረሙበት ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራሮች በአትላንታ በተዘጋጀ መርሀግብር ላይ ተቀብለዋል ተብላል። የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱ ባለፉት ዓመታት ለሰጠው የአቪዬሽን አገልግሎት እውቅና ባለፈ ዓለም አቀፍ ትብብሮችን እንዲያሰፋ…
Read More
ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሀገሯ እንዳይበር አገደች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ “ከመስከረም ወር ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል፡፡ ኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስቴር የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቀጣዩ መስከረም በኋላ ወደ አሥመራ እንዳይበር ማገዱን የሚያሳውቅ ማስታወቂያ በዛሬው እለት አውጥቷል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን አስመለክቱ በሰጠው መግለጫ፤ “የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ሐምሌ 14 2016 ዓ.ም ወይም በፈረንጆቹ 21 ጁላይ 2024 በላከው ደብዳቤ በፈረንጆቹ ከመስከረም 30 ቀን 2024 ዓ.ም. ጀምሮ አየር መንገዳችን ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ሁሉንም በረራ ማገዱን አሳውቆናል” ብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጉዳዩን አስመልክቶ የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣንን ለማግኘት ጥረት በማድረግ ላይ እንደሚገኝና ጉዳዩም በበጎ መልኩ እልባት እንደሚያገኝ ያለውን…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን የመንገደኞች ማስተናገጃ አስመረቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን የመንገደኞች ማስተናገጃ አስመረቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ50 ሚልየን ዶላር ያስገነባውን አዲስ የአገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ዛሬ አስመረቀ። በአየር መንገዱ ከአዲስ አበባ ወደ ሁሉም የአገር ውስጥ መዳረሻዎች እንዲሁም ከአገር ውስጥ ወደ አዲስ አበባ ለሚደረጉ በረራዎች በዚህ ተርሚናል አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው አዲሱ የአገር ውስጥ ተርሚናል አየር መንገዱ የሚሰጠውን የአገር ውስጥ በረራ አቅም በዕጥፍ እንደሚያሳድገው አስታውቀዋል። አየር መንገዱ 22 የአገር ውስጥ መዳረሻዎች አሉት። የቱሪዝም ሚኒስትሯ አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ አዲስ የተገነባው የአገር ውስጥ ተርሚናል የቱሪዝም ዘርፍ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልጸዋል። አየር መንገዱ ከሁለት ወራት በፊት በ55 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባውን የድጅታል ግብይት…
Read More
ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በግዛቷ እንዳያርፍ ከለከለች፡፡

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና በራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከሶስት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል። ስምምነቱ ኢትዮጵያ በኤደን ባህረ ሰላጤ 20 ኪሎሜትሮች የሚረዝም የባህር ጠረፍ እንድትከራይ እና በምትኩ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንድትሰጥ የሚያስችል ነው። ይህ ስምምነት ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል። ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የበረራ ቁጥሩ ET8372 የተሰኘ አውሮፕላን ወደ ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በዛሬው ዕለት በረራ በማድረግ ላይ እያለ እንዲመለስ መደረጉ ተገልጿል፡፡ የሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በቀድሞ ስሙ ትዊተር አሁን ኤክስ አካውንቱ ይፋ እንዳደረገው የግዛቴ አካል ናት ወደ ሚላት ሶማሊላንድ ሀርጌሳ እየበረረ የነበረ አውሮፕላን እንዳያርፍ…
Read More
የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

የኢትዮጵ አየር መንገድ ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ ጀመረ

አየር መንገዱ በአፍሪካ ያሉትን የጭነት መዳረሻዎች ብዛት ወደ 35 አሳድጓል። ወደ ካዛብላንካ የሚደረገው የጭነት በረራ ከ100 ቶን በላይ የመሸከም አቅም ባለው ቦይንግ 777-200F የእቃ ጭነት አውሮፕላን ነው ተብሏል። የኢትዮጵ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው “ወደ ካዛብላንካ ሞሮኮ አዲስ የጭነት በረራ አገልግሎት መስጠት በመጀመራችን ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል በመልዕክታቸው። ይህ በረራ መጀመሩ በአፍሪካ ያለንን የዕቃ ጭነት መዳረሻ ቁጥር 35 ሲያደርስ፤ በተመሳሳይ ብሔራዊ አየር መንገዱ በእቃ ጭነት አገልግሎት ዘርፍ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጭነት በረራ መዳረሻዎች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም የአየር የዕቃ ጭነት አገልግሎት መስክ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኝ…
Read More
ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጉዞ ቲኬት በብድር መሸጥ ጀመሩ

ዳሸን ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞች የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቅመው ክፍያውን ቆይተው የሚከፍሉበትን አዲስ የክፍያ አማራጭ በጋራ አስተዋውቀዋል። አቶ ዮሃንስ ሚሊዮን የዳሽን ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ ዋና መኮንን “ጉዞዎ ይቀድማል ክፍያው ይደርሳል” በሚል የተሰየመው ይህ አገልግሎት በደንበኞች ምርጫ መሰረት በ6 ወር ወይም በ12 ወር የብድር ክፍያ የሚሰጥ መሆኑን አመልክተዋል። ደንበኞች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለመሆን በዳሸን ባንክ የሂሳብ ቁጥር መክፈት እንደሚገባቸው እና በተጨማሪም በባንኩ ቢያንስ ለሶስት ወራት አገልግሎት ያገኙ መሆን እንደሚኖርባቸውም ጠቁመዋል።  አቶ ዮሃንስ አክለውም አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች አቅራቢያቸው ወደሚገኝ የዳሸን ባንክ ቅርንጫፍ በሚያመሩበት ወቅት አስፈላጊ ሰነዶችን ማሟላት የሚገባቸው ሲሆን ማስያዣም ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸውም ገልፀዋል። ስምምነቱን አስመልክቶ የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ብራዛቪል በረራ የጀመረበትን 40ኛ ዓመት አከበረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኮንጎ ዋና ከተማ ብራዛቪል የቀጥታ በረራ የጀመረበትን ዓመት አክብሯል፡፡ በአፍሪካ ከተመሰረተ ረጅም ዓመት ያስቆጠረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፈረንጆቹ 1983 ላይ የመጀመሪያውን የቀጥታ በረራ ወደ ብራዛቪል አድርጎ ነበር፡፡ አሁን ላይ አየር መንገዱ በሳምንት 10 በረራዎችን ከአዲስ አበባ-ብራዛቪል የደርሶ መልስ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ከ63 በላይ ከተሞች በመብረር ላይ ሲሆን ይህም ከየትኛውም የዓለማችን አየር መንገዶች በላይ በአፍሪካ ሰማይ ላይ የሚበር አየር መንገድ አድርጎታል፡፡ በታህሳስ 1945 የተመሰረተው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያ በረራውን ወደ ግብጽ ካይሮ አድርጓል፡፡ የአየር መንገዱ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዱባዩ ኤርሾው ላይ ተገኝተው እንዳሉት አየር መንገዱ ከቦይንግ እና ኤርባስ 78 አውሮፕላኖችን ለመግዛት…
Read More
በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

በቢሾፍቱ ከተማ በአምስት ቢሊዮን ዶላር አዲስ የኤርፖርት ከተማ ሊገነባ ነው

የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ አዲሱን 5 ቢሊየን ዶላር ሚያወጣ ‘የኢትዮጵያ አየር  መንገድ ከተማ’ ግንባታ በአራት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን ገለጸ፡፡ አየር መንገዱ “ኤርፖርት ሲቲ” ብሎ የሚጠራውን ግንባታ ለመጀመር ከጫፍ የደረሰው እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለማርካት መሆኑን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ የንግድ ሥራ ዘርፍ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ለማ ያደቻ ተናግረዋል፡፡ የ ‘ዓየር መንገድ ከተማው’ ካልተገነባ ዓየር መንገዱ በዘርፉ እያስመዘገበ ካለው ፈጣን ዕድገት አንጻር እንደሚፈተን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፕሮጀክቱ መታቀዱን አብራርተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 5 ቢሊየን ዶላር በጀት የተያዘለት ሲሆን፥ በዓመት 100 ሚሊየን መንገደኞችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። አሁን ላይ ዓየር መንገዱ በኦሮሚያ ክልል ከቢሾፍቱ ከተማ ጥቂት ወጣ ብሎ በሚገኝ ሥፍራ የመጀመሪያውን የ ‘ዓየር መንገድ…
Read More