SouthSudan

በጋምቤላ ክልል ባለሀብቶች ህጻናትን በከብት እየለወጡ ነው ተባለ

በጋምቤላ ክልል ባለሀብቶች ህጻናትን በከብት እየለወጡ ነው ተባለ

በጋምቤላ ክልል በደቡብ ሱዳን ሙርሌ ብሄረሰብ ታፍነው ለባርነት የሚወሰዱ ህፃናት መኖራቸውን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታውቋል። በቢሮው  የሕገ ወጥ ዝውውር ጽህፈት ቤት  አሰተባባሪ አቶ ኡቶው ቹሩ  እንደተናገሩት በዚህ መልኩ የሚወሰዱ ህፃናትን የማስመለስ ስራ ሲሰራ ቢቆይም ህገወጥ የህፃናት ዝውውርን ማስቀረት አልተቻለም ብለዋል። በደቡብ ሱዳን በኩል ያለው ድንበር  ክፍት መሆን በክልሉ ያሉ እና እድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑ ህፃናትን በህገወጥ መልኩ ለመውሰድ አመቺ እንዳደረገው ገልፀው ባለሀብቶች ህፃናቱን በከብት የሚለውጡበት ሁኔታ መኖሩም ድርጊቱን እንዳይቆም ማድረጉን ተናግረዋል። አኙዋክ ብሔረሰብ ዞንን ጨምሮ ከተለያዩ አካባቢዎች በደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ህፃናቱ እንደሚወሰዱ ተናግረዋል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከተወሰዱት ውስጥ በቅርቡ ሶስት ህፃናትን ማስመለስ መቻሉን የገለፁት አቶ ኡቶው በህይወት መኖራቸው ያልተረጋገጡ…
Read More
የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል የመንግስት ባለስልጣንን ለመግደል ሞከሩ

የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል የመንግስት ባለስልጣንን ለመግደል ሞከሩ

እንዲሁም ታጣቂዎቹ የላሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪን እንዳቆሰሉ ቢቢሲ ዘግቧል። ታጣቂዎች ተቆጣጥረውታል የተባለው አካባቢ ነዋሪዎች ወደ ሌላ ከተማ እንደሸሹም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ጎረቤት ሀገር ደቡብ ሱዳንን ከምትጎራበታቸው ክልሎች አንዱ በሆነው ጋምቤላ ታጣቂዎች ጥቃት መፈጸም የጀመሩት ከትናንት በስቲያ ከረቡዕ ሚያዝያ 22/2017 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነ አንድ የላሬ ወረዳ ኃላፊ ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ "የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጠው የገቡት" ከደቡብ ሱዳን መንግስት ጋር ግጭት ውስጥ ያሉት የሱዳን ሕዝቦች ነጻነት እንቅስቃሴ/ተቃዋሚ (Sudan People's Liberation Movement In Opposition) ታጣቂዎች ናቸው። ታጣቂዎቹ የገቡት የኑዌር ብሔረሰብ ዞን ላሬ ወረዳ ስር በምትገኘው የድንበር አካባቢዋ ፓጋግ ቀበሌ እንደሆነ ምንጩ ገልጸዋል። ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ ያሉት ታጣቂዎች ድንበሩን አቋርጠው የገቡት "ተኩስ ሲከፈትባቸው…
Read More
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ የሚዘልቅ የነዳጅ መስመር ልገነባ ነው አለች

የተትረፈረፈ የነዳጅ ሀብት ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ደቡብ ሱዳን ከዚህ በፊት ነዳጇን በሱዳን በኩል አድርጋ ለዓለም ገበያ ስታቀርብ ቆይታለች፡፡ ሱዳን በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መሆኗን ተከትሎ እስከ ፖርት ሱዳን የተዘረጋው የደቡብ ሱዳን ነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር በጦርነቱ ወድሞባታል፡፡ በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የተዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት ማቀዷ ተገልጿል፡፡ በቻይና አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ሲሳተፉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት በኢትዮጵያ በኩል እስከ ጅቡቲ ወደብ ድረስ የሚዘረጋ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዙሪያ መክረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከቻይና ብሔራዊ ነዳጅ ኮርፖሬሽን ሃላፊ ዳይ ሁሊያንግ ጋር በቤጂንግ መምከራቸውን የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ እንደ ዘገባው ከሆነ የቻይናው ነዳጅ ኮርፖሬሽን…
Read More
ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጸደቀች

ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን አጸደቀች

ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በፓርላማ በማጽደቅ ስድስተኛ ሀገር ሆናለች፡፡ የናይል ተፋሰስ አባል የሆኑ 11 ሀገራት በኡጋንዳ ኢንተቤ ባደረጉት ስምምነት የናይል ወንዝን ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ለመጠቀም የሚያስችል የጋራ ስምምነት ነው፡፡ ስምምነቱ ከ11 የናይል ተፋሰስ ሀገራት መካከል ስድስት ሀገራት በፓርላማ ካጸደቁ ቋሚ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ መግባት ይችላል ተብሏል፡፡ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ እንደገለጹት የናይል ስምምነት ማዕቀፍን በአባይ ተፋሰስ ሀገራት መካከል ከተፈረመ ቆይቷል፡፡ አምስት ሀገራት በፓርላማቸው አጽድቀው ነበር፡፡ የናይል ወንዝ ተፋሰስ ኮሚሽን ለመመስረት የሚጠበቀው ስድስተኛ ሀገር በፓርላማ እስኪያጸድቅ ድረስ ነበር፤ ደቡብ ሱዳን አጸድቃለች ብለዋል፡፡ ስድስት ሀገራት የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ማጽደቃቸው ፋይዳው ከፍተኛ ነው ያሉት አምባሳደሩ…
Read More
ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ14 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል። በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር እንደሚረዝም ታውቋል፡፡ የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡ ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች…
Read More