Kenya

ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ምርጫ በየአራት ዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት የህብረቱ ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት ስልጣን ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ ቀርቶታል፡፡ ይህን ተከትሎም ህብረቱ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በይፋ ጥያቄ አቀርበዋል፡፡ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የራይላ ኦዲንጋ ጥያቄን በአዲስ አበባ በይፋ ለአፍሪካ ህብረት አቅርቧል፡፡ የአፍሪካ ህብረት እጩ ተወዳዳሪዎች እንዲመዘገቡ ያስቀመጠው ጊዜ የፊታችን ማክሰኞ የሚያበቃ ሲሆን ኬንያ ራይላ ኦዲንጋን ዋነኛ እጩ አድርጋ አስመዘግባለች፡፡ ከኬንያ በተጨማሪ ጅቡቲ፣ ሲሸልስ እና ሶማሊያም እጩ ያስመዘገቡ ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ የተሻለ ድምጽ ሊያገኙ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ እጩዎች ከተመዘገቡ በኋላ ኢትዮጵያዊቷ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጅት ስነጊዮርጊስ አባል የሆኑት የአፍሪካ…
Read More
ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀመረች

ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀመረች

ኬንያ፣ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የላሙ ወደብን ለማልማት እና ለመጠቀም በ2001 ዓ.ም በወቅቱ የኬንያ ፕሬዝዳንት፣ ሞ ኪባኪ፣ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና በደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት አማካኝነት ስምምነት መፈራረሟ ይታወሳል፡፡ ኬንያ ይህን ፕሮጀክት በማልማት ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን እንዲጠቀሙበት ፍላጎት ያላት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ፍላጎት እንዳልነበራት ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ኢትዮጵያ ተጨማሪ የገቢ ወጪ ንግድ አማራጭ ወደብ እንዲኖራት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ሲሆን የላሙ ወደብን አንዱ አማራጭ አድርጎ ለመጠቀም መወሰኑ ከወራት በፊት መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ ስምምነት ከተፈረመ ከ15 ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀምራለች፡፡ "ዓባይ" የተሰኘችው የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ ግንቦት 3 ቀን 2016…
Read More
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለሱዳን ጅቡቲ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል በመሸጥ ላይ ስትሆን ለተጨማሪ ሀገራትም ሀይል ለመሸጥ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ ለይ ትገኛለች፡፡ ከአንድ ወር በፊት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲ የሀይል ሽያጭ ስምምነት ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ሀምሌ 2022 ላይ ለ25 ዓመት የሚዘልቅ የሀይል ሽያጭ ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት የተደረጉ የሀይል ሽያጭ ስምምነቶች ሳይመረመሩ ተጨማሪ ስምምነቶች እንዳይካሄዱ እገዳ ጥሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ በኬንያ መንግስት ላይ እገዳ ጣለው በገጠር ለሚኖረው ህዝብ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ሀይል ታሪፍ ውድ ነው በሚል ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ለኬንያ ሀይል የምትሸጠው ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ህዝቧ ውስጥ ግማሽ ያህሉ…
Read More
የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

የመጀመሪያው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀመረ

ከድርቅ ጀምሮ እስከ በርሃማነት በተደቀነባት የአፍሪካ አህጉር የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ የሚመክር የአየር ንብረት ጉባኤ በናይሮቢ መካሄድ ጀምሯል። በኬንያ አስተናጋጅነት የሚካሄደው ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ቀናት ይካሄዳልብተብሏል። በጉባኤው ላይ ከ20 ቡላይ የአፍሪካ መሪዎች፣ የበርካታ ሀገራት ሚንስትሮች፣ ልዑኮችና የአየር ንብረት ተሟጋቾች ይሳተፋሉ። በአህጉሪቱ እንደ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያና ኬንያ ባሉ ሀገራት ከ40 ዓመታት ወዲህ የከፋ የተባለ ድርቅ ተከስቷል። በዚህም በአፍሪካ ቀንድ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ዋስትና ቀውስ የተከሰተ ሲሆን፤ 10 ሚሊዮን የሚሆኑ እንስሳት ሞተዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ እንደሚለው እየጨመረ ከመጣው የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዘ በሚከሰቱ አደጋዎች ሀገራት በየዓመቱ ከሰባት እስከ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብታቸውን ያጣሉ። የአየር ንብረት ለውጥን መከላከል ካልተቻለ…
Read More
ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ከኬንያ ላሙ ወደብ ሞያሌ- አዲስ አበባ የባቡር መስመር ሊገነባ እንደሆነ ተገለጸ

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን የባቡር መስመር በ14 ቢሊዮን ዶላር ልትዘረጋ መሆኑን አስታውቃለች፡፡ ኬንያ የምትዘረጋው ይህ ፈጣን የባቡር መስመር በኤሌክትሪክ የሚሰራ ሲሆን፤ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ ላሙ ወደብ በማድረግ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን እንደሚያገናኝ ብሉምበርግ ዘግቧል። በዓይነቱ ልዩ ነው የተባለው ይህ የባቡር መስመር በፈረንጆቹ 2025 ሥራ እንደሚጀመር እና 3 ሺሕ ከሎ ሜትር እንደሚረዝም ታውቋል፡፡ የባቡር መስመሩ መነሻውን ከህንድ ውቅያኖስ አድርጎ፣ በኬንያዋ ማዕከላዊ ከተማ ኦሲዮሎን በኩል፣ ናይሮቢን እና አዲስ አበባን በማገናኘት የመጨረሻም መዳረሻውን ደቡብ ሱዳን ጁባ እንደሚያደርግ ተነግሯል፡፡ ይህ ፈጣን የባቡር መስመር “ኢትዮጵያ በአሰብ እና ምጽዋ እንዲሁም ጅቡቲ ወደቦች ላይ ያላትን ጥገኝነት የሚቀንስ ነው” የተባለ ሲሆን፤ ሌሎች በርካታ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች…
Read More
አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

ኬንያ የአፍሪካ ሀገራት የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ እና አገልግሎት ሲለዋወጡ በራሳቸው ገንዘብ ክፍያ  መፈጸም እንዲጀምሩ ጠይቃለች። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ ጅቡቲ ያመሩት የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ አፍሪካ በዶላር ላይ ያላት ጥገኝነት ይብቃ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። “ከጂቡቲ እቃ ገዝተን በዶላር የምንከፍለው ለምንድን ነው? ለምን? ምንም ምክንያት የለም”  ያሉት ፕሬዝዳንት ሩቶ ጂቡቲም ሆነች ኬንያ የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ የአሜሪካ ዶላር መጠቀም አያስፈልጋቸውም ብለዋል። “እኛ የአሜሪካን ዶላር እየተቃወምን አይደለም፤ በነጻነት ግብይት መፈጸም ስለፈለግን እንጂ” ሲሉም ስለ ዶላር አስፈላጊነት ተናግረዋል። እንደ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ዘገባ ፕሬዝዳንቱ ሩቶ አክለውም “ዶላር የሚያስፈልገን ከአሜሪካ ጋር ለምናደርገው ግብይት ብቻ ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በፈረንጆቹ 1993 የተቋቋመው የአፍሪ ኤክዚም ባንክ ግብይቱ…
Read More
ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በመሸመት ቀዳሚ አገር ሆነች

ኬንያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸመት ቀዳሚ መሆኗ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይ ባለፈው ጥር ወር ያስገባቸው የኃይል መጠን በታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሏል፡፡ ይህ የሆነውም በምስራቅ አፍሪካ ባጋጠመው አስከፊ ድርቅ ምክንያት የኃይል ማመንጫ ግድቦች ውሃቸው በመድረቁ ምክንያት መሆኑ ተነግሯል፡፡ ከኬንያ ስታትስቲክስ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ አገሪቱ ባለፈው ጥር ወር 68 ነጥብ 48 ሚሊዮን ኪሎዋት ኤሌክትሪክ ኃይል አስገብታለች፡፡ ኹለቱ አገራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የኤሌክትሪክ ኃይል በቅናሽ ለመገበያየት ከተስማሙ በኋላ፤ ኬንያ 39 ሚሊዮን ዩኒት ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ ተነግሯል፡፡ በዚህም አገሪቷ በርካሽ ዋጋ ኃይል ለማስገባት ከተስማማች በኋላ ጥር ላይ 200 ሜጋዋት የኤሌክትርክ ኃይል ከኢትዮጵያ ማስገባቷ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም የኃይል አቅርቦቱን ለማረጋጋት እንዳስቻላት ተጠቁሟል፡፡ ኬንያ…
Read More
የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

የኬንያው ኬሲቢ ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ድርሻ ለመግዛት መወሰኑን አስታወቀ

ዋና መቀመጫውን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ኬሲቢ ግሩፕ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ በመግዛት ወደ ገበያው ለመግባት አማራጮችን እየገመገመ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ባንክ የሆነው ኬሲቢ ኬንያን ጨምሮ በቡሩንዲ፣ ሩዋንዳ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ታንዛንያ እና ዲሞክራቲክ ኮንጎ በባንክ ኢንዱስትሪ እየሰራ ይገኛል። ይህ ባንክ አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ባንኮች የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት መወሰኑ ተሰምቷል። ይሁንና የኬንያው ባንክ ከየትኛው የኢትዮጵያ ባንክ አክስዮን ለመግዛት እንደወሰነ አልታወቀም። የባንኩ ፋይናንስ ዳይሬክተር የሆኑት ላውረንስ ኪማቲ ከቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ባንክ ገበያ ላይ ቅኝተ ማድረጋቸውን ገልጸው፤ ከተለያዩ ባንኮች ሰዎች ጋር መወያየታቸውንም ጠቁመዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ከእነርሱ ጋር ሊሠሩ የሚችሉትን መለየታቸውንም በቆይታቸው ተናግረዋል፡፡ እንደ ላውረንስ የባንኮቹ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም የተሻለ…
Read More