Kenya

በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር የሚኖሩ ህዝቦች ከባድ የድርቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ

በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር የሚኖሩ ህዝቦች ከባድ የድርቅ አደጋ ተጋርጦባቸዋል ተባለ

ቦረናን ጨምሮ 85 በመቶ የሚሆነው በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር አካባቢ ያለ ህዝብ በመጪው ዓመት ከባድ የድርቅና ረሃብ ስጋት እንደተጋረጠባቸው ተገልጿል። በኢትዮጵያ እና ኬንያ ድንበር ቦረና ኢትዮጵያ እና ማርሳቢት ኬንያ አካባቢ ዝናብ አጠር መሆኑና አልፎ አልፎ ሲዘንብም ጎርፍ የሚያስከትል መሆኑ ተነግሯል፡፡ ቮለንተሪ ሰርቪስ ኦቨር ሲስ(VSO)፣ ሆርን ኦፍ አፍሪካ ዴቨሎፕመንት ኢንሼቲቭ (HODI) ፣አውስትራሊያን ዴቨሎፕመንት ኮፕሬሽን እና  ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት ኤንድ ጉድ ገቨርነንስ  የተሰኙ የሲቪል ማህበራት በአካባቢው ሲሰሩ የቆዩትን የመጀመሪያ ዙር ፕሮጀክት መዝጊያ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የVSO የኢትዮጵያ ተወካይ ዶክተር ተመስገን አለሙ የአትዮጵያ ኬንያ ድንበር ከግጭት፣ ከድርቅ እና ረሃብ ባለፈ አካባቢው የአደንዛዥ ዕፅ ፣ ህገ-ወጥ የሰው ዝውውር እና ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት…
Read More
ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ኬንያ ለኡጋንዳ የባህር በር እንደምትሰጥ አስታወቀች

ከአንድ ሳምንት በፊት የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ ሀገራቸው የባህር በር ካላገኘች ከኬንያ ጋር ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ሲሉ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ በይፋ መልካም ምላሽ ሰጥታለች። የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ጎረቤቷ ለሆነችው ኡጋንዳ የባሕር በር እንደምትሠጥ አስታውቀዋል። ኡጋንዳ በኬንያ በኩል በነዳጅ ቧንቧ፣ በመንገድ እና በባቡር ሐዲድ አማካኝነት በሕንድ ውቅያኖስ ላይ የባሕር በር እንድታገኝ እናደርጋለን ብለዋል ፕሬዝዳንት ሩቶ። ኬንያ ለኡጋንዳ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ሲባል የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧዋን የሚያስተዳድረውን መንግሥታዊ ኩባንያ ከኡጋንዳ ጋር በጋራ ባለቤትነት ለመያዝ ፍቃደኛ መኾኗንም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል። ኬንያ በቻይና እርዳታ የተዘረጋውን የባቡር ሐዲዷን በቅርቡ እስከ ኡጋንዳ መዲና ካምፓላ ከተማ ድረስ እንደምትዘጋም በፕሬዝዳንቷ በኩል አስታውቃለች። ሌላኛዋ ወደብ አልባ ሀገር ኢትዮጵያ…
Read More
በኢትዮጵያ ታግቶ የነበረው ኬንያዊ ዜጋ መለቀቁ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ታግቶ የነበረው ኬንያዊ ዜጋ መለቀቁ ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአጋቾች ታግቶ የቆየው ኬንያዊ ዜጋ 3 ሚሊየን ሽልንግ ከተከፈለ በኋላ መለቀቁን ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ አስታወቁ። የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር እና በአዲስ አበባ ያሉት አምባሳደራቸው ባደረጉት ጥረት 3 ሚሊየን የኬንያ ሽልንግ ለአጋቾች ከተከፈለ በኋላ ሳሙኤል ንጃጊ የተባለው ዜጋቸው መለቀቁን ገልፀዋል። ሳሙኤል ከሳምንት በፊት በደብረ ብርሃን ከተማ ተቀጥሮ ከሚሰራበት ድርጅት ታግቶ የተወሰደ ሲሆን የኬንያ ኤምባሲ ለኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን ካሳወቀ በኋላ ድርድሮች መደረጋቸው ተዘግቧል። ዊሊያም ሩቶ 3 ሚሊየን የኬንያ ሽልንግ በአጋቾች መጠየቁን ገልፀው ሳሙኤል ይሰራበት የነበረው ድርጅት ክፍያውን መክፈሉን ገልጸዋል። ሳሙኤል ከተለቀቀ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው የኬንያ ኤምባሲ መቆየቱንና ወደ ኬንያ ሄዶ ከቤተሰቦቹ ጋር መቀላቀሉ ሲነገር ሩቶ ዜጎች…
Read More
ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ወታደራዊ ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ከ62 ዓመታት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ታሪካዊ የሚባል ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ከሁለቱ ሀገራት ባለፈ ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋትም የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተገልጿል። ስምምነቱን የኢትዮጵያ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ኢታማዦር ሹም ጄነራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ፈርመዋል። ስምምነቱ ከሃገራቱ በተጨማሪ ለቀጠናው ሰላምና ደህንነት የጎላ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ እና የኬንያ መከላከያ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ ተናግረዋል። በቀጣይም ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ የኬንያ መከላከያ በቁርጠኝነት ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ቻርልስ ሙሪዩ ካሃሪሪ መናገራቸውንም ከኢኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ኢትዮጵያና…
Read More
ከአዲስ አበባ ናይሮቢ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ተጀመረ

ከአዲስ አበባ ናይሮቢ የአውቶቡስ ትራንስፖርት ተጀመረ

አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን አስታውቋል። ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት እሁድ በይፋ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የድርጅቱ ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ማቺዮ ለቢቢሲ ተናግረዋል። "በአንድ ጉዞ 7 ሺህ 500 የኬንያ ሽልንግ ነው የምናስከፍለው። ለደርሶ መልስ ጉዞ ዋጋ 15 ሺህ የኬንያ ሽልንግ ወይም 16 ሺህ ብር ገደማ ያስከፍላል ተብሏል። ከኛ በፊት 'ሮያል አላይድ' የተሰኘ ከናይሮቢ ሞያሌ እና ሞምባሳ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተሰማራ ድርጅት አለ። ከአራት ዓመታት በፊት የተመሠረተው 'ሮያል አላይድ' እስከ ሞያሌ ከተማ ብቻ ይሠራ ነበር። በአውሮፕላን ቲኬት መወደድ ሳቢያ የአውቶብስ ትራንስፖርት ፍላጎት መኖሩን እና ይህንን ፍላጎት ሊያሟላ…
Read More
ኢትዮጵያ ለሱዳን የምትልከው ኤሌክትሪክ ሀይል 80 በመቶ ቀነሰ

ኢትዮጵያ ለሱዳን የምትልከው ኤሌክትሪክ ሀይል 80 በመቶ ቀነሰ

በሱዳን ባለው የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት፣ ኢትዮጵያ ወደ ሀገሪቱ የምትልከው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በ80 ከመቶ ያህል መቀነሱን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል፡፡ የተቋሙ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በጉዳዩ ላይ በሰጡት መግለጫ የሱዳን የሃይል መሰረተ ልማት በጦርነቱ በመጎዳቱ የታቀደውን ያህል መጠን ሀይል መላክ አለመቻሉን ገልፀዋል፡፡ አቶ ሞገስ መኮንን እንዳሉት “ከሱዳን ጋር የተደረገው ስምምነት እስከ 100 ሜጋዋት ድረስ ለመላክ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን በመጠን ደረጃ በጣም ቀንሷል፡፡ ከ10 እስከ 20 ሜጋዋት ድረስ ነው እየላክን ያለነው፡፡ ዝቅ ሲል እስከ 10 ሜጋዋት፣ ከፍ ሲል ደግሞ እስከ 20 ሜጋዋት ይሆናል የምንልከው፡፡ ይህ የሱዳን የኤሌክትሪክ ሃይል መሰረተልማት በጦርነት በመጎዳቱ የመጣ ችግር ነው፡፡ ግጭቱ በጣም ከፍተኛ በሆነ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሞያሌ የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ በሞያሌ የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለሁለት ዓመታት በዘለቀ ድርድር በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕቀፍ የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። በዚህም መሰረት በሞያሌ ድንበር ላይ ለሚደረጉ የሸቀጦች ንግድ የመጀመሪያ ጣሪያ 1 ሺህ የአሜሪካ ዶላር እንዲሆን ተወስኗል። በሞምባሳ የተጠናቀቀው ይህ ስምምነት የንግድ ሂደቶችን በማቅለል የድንበር ማህበረሰቦችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማሳደግ ያለመ ነው። በስምምነቱ የኢትዮጵያ የድንበር ንግድ ዞን ከሞያሌ በ50 ኪሎ ሜትር እንዲሁም የኬንያ ደግሞ በ100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚወሰን ነው። ነጋዴዎችም በጋራ በተስማሙበት የምርት ዝርዝር መሰረት እስከ 1 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የንግድ ልውውጥ በወር እስከ አራት ጊዜ ድረስ ማካሄድ ይችላሉ ተብሏል። ይህ ስምምነት የንግድ ዋጋ ጣሪያዎችን፣ የጉዞ ድግግሞሽን እና የድንበር…
Read More
ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

ራይላ ኦዲንጋ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽነር ለመሆን እጩ ሆነው ተመዘገቡ

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ምርጫ በየአራት ዓመቱ የሚካሄድ ሲሆን ላለፉት ሰባት ዓመታት የህብረቱ ሊቀመንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሃማት ስልጣን ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ ቀርቶታል፡፡ ይህን ተከትሎም ህብረቱ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን የኬንያ ፕሬዝዳንት ለመሆን አራት ጊዜ ተወዳድረው የተሸነፉት ራይላ ኦዲንጋ በይፋ ጥያቄ አቀርበዋል፡፡ የኬንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም የራይላ ኦዲንጋ ጥያቄን በአዲስ አበባ በይፋ ለአፍሪካ ህብረት አቅርቧል፡፡ የአፍሪካ ህብረት እጩ ተወዳዳሪዎች እንዲመዘገቡ ያስቀመጠው ጊዜ የፊታችን ማክሰኞ የሚያበቃ ሲሆን ኬንያ ራይላ ኦዲንጋን ዋነኛ እጩ አድርጋ አስመዘግባለች፡፡ ከኬንያ በተጨማሪ ጅቡቲ፣ ሲሸልስ እና ሶማሊያም እጩ ያስመዘገቡ ሲሆን ራይላ ኦዲንጋ የተሻለ ድምጽ ሊያገኙ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ እጩዎች ከተመዘገቡ በኋላ ኢትዮጵያዊቷ ዲፕሎማት አምባሳደር ቆንጅት ስነጊዮርጊስ አባል የሆኑት የአፍሪካ…
Read More
ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀመረች

ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀመረች

ኬንያ፣ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የላሙ ወደብን ለማልማት እና ለመጠቀም በ2001 ዓ.ም በወቅቱ የኬንያ ፕሬዝዳንት፣ ሞ ኪባኪ፣ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና በደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት አማካኝነት ስምምነት መፈራረሟ ይታወሳል፡፡ ኬንያ ይህን ፕሮጀክት በማልማት ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን እንዲጠቀሙበት ፍላጎት ያላት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ፍላጎት እንዳልነበራት ተገልጿል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ኢትዮጵያ ተጨማሪ የገቢ ወጪ ንግድ አማራጭ ወደብ እንዲኖራት የተለያዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ሲሆን የላሙ ወደብን አንዱ አማራጭ አድርጎ ለመጠቀም መወሰኑ ከወራት በፊት መግለጻቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ ስምምነት ከተፈረመ ከ15 ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የላሙ ወደብን መጠቀም ጀምራለች፡፡ "ዓባይ" የተሰኘችው የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ ግንቦት 3 ቀን 2016…
Read More
ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለሱዳን ጅቡቲ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል በመሸጥ ላይ ስትሆን ለተጨማሪ ሀገራትም ሀይል ለመሸጥ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ ለይ ትገኛለች፡፡ ከአንድ ወር በፊት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲ የሀይል ሽያጭ ስምምነት ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ሀምሌ 2022 ላይ ለ25 ዓመት የሚዘልቅ የሀይል ሽያጭ ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት የተደረጉ የሀይል ሽያጭ ስምምነቶች ሳይመረመሩ ተጨማሪ ስምምነቶች እንዳይካሄዱ እገዳ ጥሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ በኬንያ መንግስት ላይ እገዳ ጣለው በገጠር ለሚኖረው ህዝብ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ሀይል ታሪፍ ውድ ነው በሚል ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ለኬንያ ሀይል የምትሸጠው ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ህዝቧ ውስጥ ግማሽ ያህሉ…
Read More