electricityexport

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን የሀይል ሽያጭ ውል ልትሰርዝ እንደምትችል ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሶስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለሱዳን ጅቡቲ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል በመሸጥ ላይ ስትሆን ለተጨማሪ ሀገራትም ሀይል ለመሸጥ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ ለይ ትገኛለች፡፡ ከአንድ ወር በፊት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲ የሀይል ሽያጭ ስምምነት ተፈራርመው መመለሳቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ሀምሌ 2022 ላይ ለ25 ዓመት የሚዘልቅ የሀይል ሽያጭ ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ከዚህ በፊት የተደረጉ የሀይል ሽያጭ ስምምነቶች ሳይመረመሩ ተጨማሪ ስምምነቶች እንዳይካሄዱ እገዳ ጥሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ በኬንያ መንግስት ላይ እገዳ ጣለው በገጠር ለሚኖረው ህዝብ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ሀይል ታሪፍ ውድ ነው በሚል ነው፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ለኬንያ ሀይል የምትሸጠው ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ህዝቧ ውስጥ ግማሽ ያህሉ…
Read More
ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ጎረቤት ሀገር ሱዳን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ከሚገዙ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን ለዓመታት የተጠቀመችበትን እዳ አልከፈለችም ተብሏል፡፡ ሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ የተጠቀመችበትን 70 ሚሊዮን ዶላር እዳዋን ባለመክፈሏ ምክንያትም የሚቀርብላት የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በ50 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡ ካሳለፍነው ሚያዚያ ወር ጀምሮ በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሱዳን ከ8 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ግብጽ  እና ቻድ ደግሞ ሱዳናዊያን የተጠለሉባቸው ሀገራት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው የኤሌክትሪክ ሽያጭ 66 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 47 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የፌደራል ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል። ሱዳን ባለባት የጸጥታ ችግር ምክንያት ከዚህ በፊት የተጠቀመችበትን የኤሌክትሪክ ኃይል ክፍያ በወቅቱ መክፈል አለመቻሏ ለገቢው…
Read More