14
Oct
ታርኮ አቪዬሽን የተሰኘው ተቋም ከሱዳን ጊዜያዊ የአስተዳድር ዋና ከተማ ከሆነችው ፖርቱ ሱዳን ወደ አዲስ አበባ የቀጥታ በረራ ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል። የቀጥታ በረራው ከጥቅምት 20 ጀምሮ እንደሚጀመር የኩባንያው ክልላዊ ስራ አስኪያጅ ኦማር አህመድ እድሪስ ገልጸዋል። እንደ ኦማር አህመድ ገለጻ የታርኮ አቪዬሽን ቀጥታ በረራ መጀመር የኩባንያው አድማሱን ለማስፋት የያዘው እቅድ ነው። የቀጥታ በረራው በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለውን የንግድ ትብብር ከመጨመሩ ባለፈ ለነጋዴዎች፣ ኢንቨስተሮች እና ተጓዦችም ልዩ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል። ታርኮ አቪዬሽን ከፖርት ሱዳን- አስመራ የቀጥታ በረራ ያለው ሲሆን አዲሱ ከፖርት ሱዳን- አዲስ አበባ የቀጥታ በረራ የኩባንያውን ተደራሽነት ያሰፈዋልም ተብሏል። ስራ አስኪያጁ አክለውም ታርኮ አቪዬሽን ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እና ደህንነት ዋነኛ ትኩረቶች…