Egypt

የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው አዲስ አበባ ገቡ

የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው አዲስ አበባ ገቡ

ላዳው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ሌሎች የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ለመምከር ባደረጉት ጉዞ የአሜሪካ አፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዳግቪን አንደርሰንን አስከትለው አዲስ አበባ ገብተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው እና የአሜሪካ አፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዳግቪን አንደርሰን በኢትዮጵያ አየር ኃይል የተዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የአቭዬሽን ኤክስፖ መጎብኘታቸውን የመከላከያ ሚኒስቴር በፌስቡክ ገጹ ከምስል ጋር አጋርቷል። ኢትዮጵያ እና ግብጽን ጨምሮ አራት የአፍሪካ ሀገራትን በመጎብኘት ላይ ያሉት ክርስቶፈር ላንዳው በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ላንዳው በዛሬው ዕለት የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት እያከበረ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር ሀይል አቪዬሽን ኤክስፖ ጎብኝተዋል ተብሏል፡፡ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ…
Read More
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ3ኛ ጊዜ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ወጪ አሜሪካ መሸፈኗን ተናገሩ

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ3ኛ ጊዜ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ወጪ አሜሪካ መሸፈኗን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን የመጡበትን አንደኛ ዓመት አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወጪ በሀገራቸው መሸፈኑን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ላይ በቆዩባቸው ጊዜያት ስምንት ጦርነቶችን እንዳስቆሙ ገልጸው ኢትዮጵያ እና ግብጽም በህዳሴው ግድብ ምክንያት ሊያደርጉት የነበረውን ጦርነት ማስቆማቸውን ገልጸዋል። "ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ በገነባችው ትልቅ ግድብ ምክንያት ግብጾች ተጎድተዋል፣ ውሀቸው ቀንሶባቸዋል፣ ናይል ግብጽ ውስጥ ያለ ነበር እሚመስለኝ፣ ወንዙ ይህን ጉዳይ መፍታት እፈልጋለሁ" ብለዋል ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ። "የግድቡን ግንባታ ወጪ ማን እንደሸፈነው ታውቃላችሁ? እኛው ነን" ያሉት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢትዮጵያ እና ግብጽ መካከል ያለውን አለመግባባት የመፍታት እቅድ እንዳላቸውም ተናግረዋል። ስለ ኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የሚሰሙት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዚህ በፊትም…
Read More
ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ግብፅ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ እያደረገች ያለችውን ጫና ኢትዮጵያ በስጋት አንደማትመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ ግብፅ የታላቁ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ የዲፕሎማሲ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ለኢትዮጵያ ስጋት አይሆንም ሲል ተናግሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የግብፅ አካሄድ ስጋት የማይሆነው ከዚህ ቀደምም የነበረ ስለሆነ ነው ብለዋል። የህዳሴ ግድቡ ምርቃት መቃረቡን ያስታወሱት አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የቅኝ ግዛት እሳቤዎች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል። በለፉት 14 ዓመታት በመላው ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ከፍተኛ መሰናክሎችን አልፎ ህዳሴ ግድቡ የመመረቅያው ዋዜማ ላይ እንገኛለን ያሉት አምባሳደሩ ምርቃቱንም ኢትዮጵያዊያን  እና የኢትዮጵያን በጎ የሚመኙ አብረውን የሚያከብሩት  ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ለምርቃቱ በስም ያልዘረዘሯቸው እንግዶች እንደተጋበዙ…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ በሶማሊያ የቀረበባትን ክስ ውድቅ አደረገች

ከአንድ ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ስምምነቱን ተከትሎ ሶማሊያ ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ነው በሚል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አቋርጣም ነበር፡፡ የሁለቱም ሀገራት ወዳጅ የሆነችው ቱርክ በአንካራ የውይይት መድረክ ያዘጋጀች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በአንካራ መስማማታቸውን ከሁለት ሳምንት በፊት ተናግረው ነበር፡፡ በቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የተስማሙት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አንዳቸው የሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ለማክበር ኢትዮጵያም የወደብ አገልግሎት ከሶማሊያ እንደምታገኝ ተስማምተውም ነበር፡፡ ከአንካራው ስምምነት በኋላ የሶማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ እና የደህንነት ባለስልጣናት ወደ አዲስ አበባ መጥተው ተወያይተዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ሬድዋን ሁሴን የሶማሊያ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት…
Read More
ሶማሊላንድ በሀርጌሳ የሚገኘው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍትን ዘጋች

ሶማሊላንድ በሀርጌሳ የሚገኘው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍትን ዘጋች

ራስ ገዟ ሶማሊላንድ በሀርጌሳ ያለው የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍት በቋሚነት እንዲዘጋ መወሰኗን ገልጻለች፡፡ የሶማሊላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ አካውንቱ ለይ እንዳስታወቀው በሀርጌሳ ያለው የግብጽ ቤተ መጽሃፍት እንዲዘጋ የተወሰነ ሲሆን የቤተ መጽሀፍት ቤቱ ሰራተኞችም በ72 ሰዓት ውስጥ ሀርጌሳን ለቀው እንዲወጡ ታዘዋል፡፡ እንደ ሚኒስቴሩ መግለጫ ሶማሊላንድ ይህንን እርምጃ የወሰደችው ከደህንነት ጋር በተያያዘ ነው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢሳ ክዛ ሞሀሙድ ተቀማጭነታቸው በሀርጌሳ ላደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች ስለ ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያ የወደብ ስምምነት ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሚኒስትሩ ለዲፕሎማቶቹ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረጉት የወደብ መግባቢያ ስምምነት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን እና በቅርቡ የትግበራ ስምምነት እንደደረግ መናገራቸው ተገልጿል፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም “የግብጽ ጦር በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ መግባቱ…
Read More
ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ኢትዮጵያ በጸጥታው ምክር ቤት በግብጽ ለቀረበባት ክስ ምላሽ ሰጥታለች ከአንድ ሳምንት በፊት ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስተኛው ዙር ውሃ ሙሌት ማከናወኗ እና ተጨማሪ ተርባይኖች ሀይል ማመንጨት መጀመራቸውን ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም ግብጽ ኢትዮጵያ በግድቡ ለይ የተናጠል እርምጃ ወስዳለች በሚል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ክስ አስገብታለች፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተፈረመው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2015 የተፈረመውን የመርህ ስምምነት ጥሳለች፣ ድርጊቱም ለአካባቢው ሀገራት አለመረጋጋት የሚሆን ነው፣ ግብጽ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በተመድ ቻርተር አማካኝነት እርምጃ ትወስዳለች ሲልም ያትታል፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ለቀረበባት ክስ በይፋ ባሳለፍነው ቅዳሜ ለተመድ ይፋዊ ምላሽ መስጠቷን አል ዐይን ከታማኝ ምንጮች አረጋግጧል፡፡ አል ዐይን የተመለከተው ይህ ደብዳቤ…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ በኩል ጦሯን ዝግጁ ማድረጓን ገለጸች

ኢትዮጵያ በሶማሊያ በኩል ጦሯን ዝግጁ ማድረጓን ገለጸች

የኢትዮጵያ አየር ሀይል ከሶማሊያ ጋር የምትዋሰንበት ምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታውቋል ከሰሞኑ ግብፅ እና ሶማልያ በቀጠናው እያረጉት ያለውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር ሀይል የምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ እንደሚገኝ ገልጿል። በኢትዮጵያ አየር ሃይል የ3ኛው አየር ምድብ የተሰጠውን ሃገራዊ ግዳጅና ተልዕኮ ለመወጣት በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የአየር ምድቡ አዛዥ ኮሎኔል ደረጀ ቡሽሬ ገልፀዋል፡፡ አዛዡ የ3ኛው አየር ምድብ የሃገራችንን ብሎም የምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ የሚገኝ የሃገር መከታና መመኪያ የሆነ ምድብ ነው ያሉ ሲሆን "ወደፊትም ኢትዮጵያን ከውስጥም ይሁን ከውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ለመጠበቅ በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል" ብለዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር የምስራቅ ዕዝ በተሟላ…
Read More
ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ተቃውሞ አለኝ የምትለው ግብጽ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሳለች፡፡ ግብጽ በዛሬው ዕለት ለጸጽታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸችው ኢትዮጵያ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ለአምስተኛ ዓመት ውሃ ሙሌት አከናውናለች ይላል፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ስደተኞች እና ግብጻዊያን አርበኞች እንደተጻፈ የተገለጸው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ የግብጻዊያንን ጥቅም በሚጻረር መልኩ የውሃ ሙሌት እያካሄደች ነው ብሏል፡፡ በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደል አቲ የተፈረመው ይህ የተመድ ደብዳቤ ኢትዮጵያ፣ግብጽ እና ሱዳን በፈረንጆቹ 2015 ላይ የተፈራረሙትን ስምምነት በመጣስ የግድቡ ውሃ ሙሌት በተናጠል ተከናውኗል፣ ይህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን ጥቅም የሚጎዳ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የግድቡን…
Read More
ኢትዮጵያ በሶማሊያ መወረሯን እንደማትረሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ

ኢትዮጵያ በሶማሊያ መወረሯን እንደማትረሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ታዬ አጽቀስላሴ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ሚንስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት የሶማሊያ መንግሥት ውስጥ ያሉ የተወሰኑ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ያልተገባ ስም ማጥፋት ስራ እየሰሩ ነው ብለዋል። ሶማሊያ እንደ ሉዓላዊ ሀገር ከየትኛውም ሀገር ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መመስረት መብቷ ቢሆንም "ይህ የሚሆነው ግን ለሌላ ሀገር ስጋት በማይሆን መልኩ ነው" ሲሉም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "በሶማሊያ ያለውን መንግሥት ያቋቋምነው እኛ ነን" ያሉት አምባሳደር ታዬ ይህን ያደረግነው አልሻባብ ስልጣን ቢይዝ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለአካባቢው ሀገራት ስጋት እንደሚሆን ስለምናምን ነውም ብለዋል። የሶማሊያ ሰላም እኛን ይመለከታል፣ ሰላም እንዲመጣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መስዋዕትነት ከፍሏል፣ አሁንም የሶማሊያ ሁኔታ የሚያሳስበን ድንበር ዘሎ የሚመጣ ትርምስን ስለማንፈልግ ነውም…
Read More
ኢትዮጵያ ሶማሊያ ቀጠናውን ለማተራመስ ከውጭ ሃይሎች ጋር እየተባበረች ነው ስትል ከሰሰች

ኢትዮጵያ ሶማሊያ ቀጠናውን ለማተራመስ ከውጭ ሃይሎች ጋር እየተባበረች ነው ስትል ከሰሰች

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በሶማሊያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አሳሳቢ ነው ብሏል። ሚኒስቴሩ መግለጫውን ያወጣው ግብጽ ከሶስት አስርት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ መላኳ ከተነገረ በኋላ ነው። ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር በተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት ከሶማሊያ ጋር ግንኙነቷ ሲሻክር፥ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር ቅራኔ ውስጥ ያለችው ግብጽ ለሶማሊያ ድጋፏን አሳይታለች። ግብጽ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ከሞቃዲሾ ጋር የወታደራዊ ደህንነት ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን በሶማሊያ ለሚሰማራው አዲስ የሰላም አስከባሪ ተልእኮ ወታደሮች ለመላክ ፈቃደኝነቷን መግለጿም ይታወሳል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው ግብጽን በስም ባይጠቅስም በሶማሊያ የተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (አትሚስ) ሽግግር ሂደት ሳይጠናቀቅ በሞቃዲሾ አዲስ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ…
Read More