24
Dec
ከአንድ ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ጋር የወደብ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል፡፡ ስምምነቱን ተከትሎ ሶማሊያ ሉዓላዊነቴን የሚጥስ ነው በሚል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት አቋርጣም ነበር፡፡ የሁለቱም ሀገራት ወዳጅ የሆነችው ቱርክ በአንካራ የውይይት መድረክ ያዘጋጀች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በአንካራ መስማማታቸውን ከሁለት ሳምንት በፊት ተናግረው ነበር፡፡ በቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት የተስማሙት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አንዳቸው የሌላኛቸውን ሉዓላዊነት ለማክበር ኢትዮጵያም የወደብ አገልግሎት ከሶማሊያ እንደምታገኝ ተስማምተውም ነበር፡፡ ከአንካራው ስምምነት በኋላ የሶማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ እና የደህንነት ባለስልጣናት ወደ አዲስ አበባ መጥተው ተወያይተዋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ሬድዋን ሁሴን የሶማሊያ ብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት…