GERD

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመረቀች

ኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብን አስመረቀች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኬንያው ፕሬዚዳንት ውሊያም ሩቶ፣ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት እስማኢል ኦማር ጊሌ፣ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር በተገኙበት የዓባይ ግድብ መርቀዋል። የኢትዮጵያ የዓባይ ግድብ የምረቃ ሥነስርዓት ዛሬ ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓም ሲካሄድ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል። የዓባይ ግድብ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ 233 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደገ ሲሆን፤ ቦንድ በመግዛት፤ ስጦታ በመስጠት እና በሌሎች መንገዶች ህዝብ ትልቅ ተሳትፎ እንዳደረገ በስፋት ተግልጿል፡፡ ከአምስት ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተደረገበት የህዳሴ ግድቡ መጠናቀቅም የኢትዮጵያን አቅም በሁሉም ዘርፍ የሚያሳግ እንደሆነም የተለያዩ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ዓባይ ግድብ የሚገኘው በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ…
Read More
ለህዳሴው ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ

ለህዳሴው ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 233 ቢልዮን ብር ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የተቋሙ የኮርፖሬት የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ለህዳሴ ግድብ ግንባታ በአጠቃለይ 233 ቢልዮን ብር ወጪ ተደርጓል። ከዚህ ውስጥ 223 ቢልዮን ወይም 91 በመቶ የሚሆነው ወጪ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተገኘ ነው ብለዋል። ከመላው ኢትዮጵያዊያን በቦንድ ግዢ 18 ነጥብ 9 ቢልዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን፤ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን 1 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር መሰብሰቡንም አቶ ሞገስ አብራርተዋል። እንዲሁም 3 ነጥብ 2 ቢልዮን ብር በስጦታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። ላለፉት 14 ዓመት በግንባታ ላይ…
Read More
በህዳሴው ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ኢትዮጵያዊያን መሞታቸው ተገለጸ

በህዳሴው ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ኢትዮጵያዊያን መሞታቸው ተገለጸ

የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስትር ሀብታሙ ኢተፋ ከሪፖርተር መጽሄት ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ላይ እንዳሉት በታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ህይወታቸውን ካጡ ዜጎች መካከል የቀድሞው የግድቡ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ አንዱ ሲሆኑ ለብቻቸው መታሰቢያ ሀውልት እንደማይቆምላቸውም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "የጸጥታ ሀይሎች፣ ሹፌሮች፣ ሰራተኞች እና ሌሎሽም የህብረተሰብ ክፍሎች ህይወታቸውን አጥተዋል ስለዚህ ይህ በሆነበት ሁኔታ ለግለሰቦች የተለየ መታሰቢያ ሀውልት የለም" ሲሉም ሚንስትሩ በቃለ መጠይቁ ወቅት ገልጸዋል። በግዝፈቱ ከአፍሪካ ቁጥር አንድ የሆነው የህዳሴው ግድብ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚመረቅ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሰሞኑ በኢትቪ በተላለፈ ንግግራቸው ለግድቡ ግንባታ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል። የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር…
Read More
ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ኢትዮጵያ ግብጽን በስጋትነት እንደማትመለከታት ገለጸች

ግብፅ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ እያደረገች ያለችውን ጫና ኢትዮጵያ በስጋት አንደማትመለከተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ ግብፅ የታላቁ ህዳሴ ግድቡን በተመለከተ የዲፕሎማሲ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ለኢትዮጵያ ስጋት አይሆንም ሲል ተናግሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የግብፅ አካሄድ ስጋት የማይሆነው ከዚህ ቀደምም የነበረ ስለሆነ ነው ብለዋል። የህዳሴ ግድቡ ምርቃት መቃረቡን ያስታወሱት አምባሳደር  ነቢያት ጌታቸው የቅኝ ግዛት እሳቤዎች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል። በለፉት 14 ዓመታት በመላው ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ ከፍተኛ መሰናክሎችን አልፎ ህዳሴ ግድቡ የመመረቅያው ዋዜማ ላይ እንገኛለን ያሉት አምባሳደሩ ምርቃቱንም ኢትዮጵያዊያን  እና የኢትዮጵያን በጎ የሚመኙ አብረውን የሚያከብሩት  ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ለምርቃቱ በስም ያልዘረዘሯቸው እንግዶች እንደተጋበዙ…
Read More
ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ሀገራቸው አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስተያየት ውድቅ አድርጓል። የጽህፈት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ ፕሬዝዳንቱ ቱርዝ ሶሻል ተብሎ በሚጠራው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዩናይትድ ስቴትስ የህዳሴ ግድብን በገንዘብ ደግፋለች ማለታቸውን "መሠረተ ቢስ" ብለውታል። ኃላፊው "ህዳሴ ግድብ ከ20ዐ3 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት፣ ጉልበት፣ እውቀትና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለ ነው” ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል። አክለውም የአሜሪካው መሪ ንግግር ከዓለም አቀፋ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተናግረዋል። ከ15 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሁለት ወር በኋላ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተገለጸ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከቀጣዩ መስከረም ወር ጀምሮ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ መናገራቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘግቧል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ካሉ የሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ከመስከረም ወር ጀምሮ ነዳጇን ለገበያ ማቅረብ እንደምትጀምር ገልጸዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰባት ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪክ ነዳጅ ማውጣት ጀመረች በሚል ለኢትዮጵያዊያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡ ይሁንና ይህ ከሆነ ከሰባት ዓመት በኋላ ኢትዮጵያ ነዳጅ ለገበያ እንደምታቀርብ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሶማሊ ክልል ኦጋዴን አካባቢ ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ እንዳላት በተደጋጋሚ ሲገለጽ የቆየ ሲሆን የቻይና ፖሊሲጂኤል ኩባንያ ነዳጅ ለማውጣት በሂደት ላይ ነበር፡፡ ኢትዮጵያ የነዳጅ ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ…
Read More
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ከ15 ዓመት በፊት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ግንባታው የተጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በያዝነው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ውቅት እንዳሉት ህዳሴ ግድብን ከ6 ወር በኋላ እንመርቃለን ብለዋል፡፡ መንግስት ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ መንግስት ጋር በተለይም ከደህንነት መስሪያ ቤት ጋር ህዳሴን በተመለከተ ውይይት አድርገናል የተለያዩ ሃሳቦችም በህዳሴ ግድብ ዙሪያ አቅርበናል ብለዋል፡፡ መንግስት በህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ዝግጁ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል:: የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ 15 ዓመታት ሊሞሉት አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።…
Read More
የህዳሴው ግድብን ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

የህዳሴው ግድብን ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተባለ

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ቀሪ ስራዎች ለማጠናቀቅ 80 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ተገልጿል፡፡ ከ14 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ ግድብ፤ ግንባታው 97.6 በመቶ እንደደረሰና ጥቂት የማጠናቀቂያ ስራዎች ብቻ እንደቀሩት  የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ የፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ተናግሯል፡፡ ህዝቡ እስካሁን ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ ለግእቡ ግንባታ በበጎ ፈቃደኝነት ያዋጣ ሲሆን በዚህ ዓመት 1.6 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የዚህ አካል የሆነና ባንኮችን፣ ኢንሹራንስ ተቋማትንና የብድርና ቁጠባ ተቋማትን ያሳተፈ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ባሳለፍነው ዓርብ አካሂዷል፡፡ በመርሃ ግብሩ 110 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ የታሰበ ቢሆንም በወቅቱ ከተቋማቱ መሰብሰብ የተቻለው 25.9 ሚሊዮን ብር ብቻ…
Read More
ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ ፕሮጀክቶችን እንዳትገነባ ኢትዮጵያ ጠየቀች

ኢትዮጵያ በጸጥታው ምክር ቤት በግብጽ ለቀረበባት ክስ ምላሽ ሰጥታለች ከአንድ ሳምንት በፊት ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስተኛው ዙር ውሃ ሙሌት ማከናወኗ እና ተጨማሪ ተርባይኖች ሀይል ማመንጨት መጀመራቸውን ይፋ ማድረጓ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም ግብጽ ኢትዮጵያ በግድቡ ለይ የተናጠል እርምጃ ወስዳለች በሚል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ክስ አስገብታለች፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተፈረመው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2015 የተፈረመውን የመርህ ስምምነት ጥሳለች፣ ድርጊቱም ለአካባቢው ሀገራት አለመረጋጋት የሚሆን ነው፣ ግብጽ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ በተመድ ቻርተር አማካኝነት እርምጃ ትወስዳለች ሲልም ያትታል፡፡ ኢትዮጵያ በግብጽ ለቀረበባት ክስ በይፋ ባሳለፍነው ቅዳሜ ለተመድ ይፋዊ ምላሽ መስጠቷን አል ዐይን ከታማኝ ምንጮች አረጋግጧል፡፡ አል ዐይን የተመለከተው ይህ ደብዳቤ…
Read More
ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

ግብጽ በድጋሚ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሰሰች

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ተቃውሞ አለኝ የምትለው ግብጽ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ላይ ከሳለች፡፡ ግብጽ በዛሬው ዕለት ለጸጽታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸችው ኢትዮጵያ በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ለአምስተኛ ዓመት ውሃ ሙሌት አከናውናለች ይላል፡፡ በግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ስደተኞች እና ግብጻዊያን አርበኞች እንደተጻፈ የተገለጸው ይህ ደብዳቤ ኢትዮጵያ የግብጻዊያንን ጥቅም በሚጻረር መልኩ የውሃ ሙሌት እያካሄደች ነው ብሏል፡፡ በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደል አቲ የተፈረመው ይህ የተመድ ደብዳቤ ኢትዮጵያ፣ግብጽ እና ሱዳን በፈረንጆቹ 2015 ላይ የተፈራረሙትን ስምምነት በመጣስ የግድቡ ውሃ ሙሌት በተናጠል ተከናውኗል፣ ይህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን ጥቅም የሚጎዳ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የግድቡን…
Read More