US-Ethiopia

የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው አዲስ አበባ ገቡ

የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው አዲስ አበባ ገቡ

ላዳው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና ሌሎች የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ለመምከር ባደረጉት ጉዞ የአሜሪካ አፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዳግቪን አንደርሰንን አስከትለው አዲስ አበባ ገብተዋል። የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የአሜሪካ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፎር ላንዳው እና የአሜሪካ አፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዳግቪን አንደርሰን በኢትዮጵያ አየር ኃይል የተዘጋጀውን ዓለም አቀፍ የአቭዬሽን ኤክስፖ መጎብኘታቸውን የመከላከያ ሚኒስቴር በፌስቡክ ገጹ ከምስል ጋር አጋርቷል። ኢትዮጵያ እና ግብጽን ጨምሮ አራት የአፍሪካ ሀገራትን በመጎብኘት ላይ ያሉት ክርስቶፈር ላንዳው በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ ላንዳው በዛሬው ዕለት የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት እያከበረ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር ሀይል አቪዬሽን ኤክስፖ ጎብኝተዋል ተብሏል፡፡ ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአፍሪካ…
Read More
አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፕሬዝዳንት ትራምፕ አቀባበል ተደረገላቸው

አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፕሬዝዳንት ትራምፕ አቀባበል ተደረገላቸው

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተ-መንግሥት ተገናኝተው ተወያይተዋል ። በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተ-መንግሥት ተገናኝተው ተወያይተዋል። አምባሳደር ብናልፍ ነጩ ቤተ-መንግሥት ሲደርሱ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀባበል እንደተደረገላቸው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ይህ የመጀመሪያ ግንኙነት በቀጣይ ጊዜያት ለሚደረጉ ውይይቶች መጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል የተባለም ሲሆን፤ አምባሳደሩ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር ተገናኝተው ስላደረጉት ውይይት በይፋ የተገለጸ ነገር የለም ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን፤ በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ሰላም፣ ጸጥታና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ከመፍጠር አንጻር ያሉ ዕድሎችም ሰፊ…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የእርዳታ እቀባ እንደምታነሳ ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የጣለችውን የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ልታነሳ መሆኑ ተዘገበ ለሁለት ዓመታት ሲካሄድ ቆይቶ በተያዘው ዓመት ጥቅምት ወር መቋጫ ባገኘው የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ጦርነት ከመንግሥት ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቶ የቆየው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የቆየውን የእርዳታ እና የፋይናንስ ድጋፍ እቀባ ሊያነሳ መሆኑን መስማቱን የዘገበው ፎሬን ፖሊሲ ነው፡፡ መጽሔቱ ከባለሥልጣናት ሰምቼዋለሁ ባለው መረጃ መሠረት የባይደን አስተዳደር እቀባውን ማንሳቱን በቅርቡ አዲስ አበባ ያቀናሉ በተባሉት የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ አንቶንዮ ብሊንክን በኩል ይፋ ያደርጋል፡፡ በሰሜኑ ጦርነት ተደጋጋሚ መግለጫዎችን ስታወጣ የቆየችውና በመንግሥት እና ሕወሓት የሠላም ስምምነት ሒደት ከፍተኛ ሚና የነበራት አሜሪካ፤ ጦርነቱ በተጀመረበት 2013 ግንቦት ወር ላይ ነበር…
Read More