DonaldTrump

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የ10 በመቶ ቀረጥ ጣለች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የ10 በመቶ ቀረጥ ጣለች

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ ታሪፍ እንዲጣል ያዘዙ ሲሆን ኢትዮጵያም ወደ አሜሪካ በምትልካቸው ምርቶች ላይ የ10 በመቶ ቀረጥ ተጥሎባታል። ፕሬዚዳንቱ በነጩ ቤተ መንግሥት በሰጡት መግለጫ አሜሪካ ከሌሎች ሀገራት ጋር በምታደርገው የንግድ ልውውጥ ላይ አዲስ የታሪፍ መጠኖችን መጣላቸውን አስታውቀዋል። እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ እርምጃው አሜሪካን ቀዳሚ ለማድረግ እና የንግድ ጉድለትን ለመቀነስ ያለመ ነው። በአብዛኛዎቹ ሀገራት ላይ የተጣለው ታሪፍ ከ10% እስከ 49% የሚደርስ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም 10% ታሪፍ ተጥሎባታል። ኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ ከተሞች አበባ፣ ቡና፣ የቆዳ እና አልባሳት ምርቶችን በመላክ ላይ ስትሆን ተጨማሪ 10 በመቶ ቀረጥ ለመክፈል ትገደዳለች። አሜሪካ የንግድ ጉድለቷን ለመቀነስ እና የአሜሪካን ኢኮኖሚ ለመጠበቅ ይህን እርምጃ እንደወሰደች የገለፁት…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለዶናልድ ትራምፕ እነኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለዶናልድ ትራምፕ እነኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር የሆነችው አሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ሲሆን የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ እየመሩ ገኛሉ፡፡ ትራምፕ እስካሁን በተረጋገጡ የወኪል መራጮች ምርጫ አማካኝነት 267 በ224 ድምጽ እየመሩ ይገኛሉ፡፡ አስቀድሞ 270 የወኪል መራጮችን ድምጽ ያገኘ እጩ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ይሆናል በሚለው ህግ መሰረት ዶናልድ ትራምፕ በይፋ ማሸነፋቸውን ለማወጅ ሶስት ድምጽ ብቻ መቅረቱን ተከትሎ በርካታ የዓለማችን ሀገራት አስቀድመው እንኳን ደስ አለዎት መልዕክታቸውን እያስተላለፉ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አንዱ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕ ምርጫውን ስላሸነፉ እንኳን ደስ አለዎት፣ ወደ መሪነት እንኳን ድጋሚ መጡ አብረን እንደምንሰራ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል፡፡ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በበኩላቸው ለዶናልድ ትራምፕ እና ባለቤታቸው እንኳን ወደ…
Read More