26
Jun
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሳምንት ሀገራቸው አሜሪካ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጓን ተናግረዋል። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አስተያየት ውድቅ አድርጓል። የጽህፈት ቤቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አረጋዊ በርሔ ፕሬዝዳንቱ ቱርዝ ሶሻል ተብሎ በሚጠራው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዩናይትድ ስቴትስ የህዳሴ ግድብን በገንዘብ ደግፋለች ማለታቸውን "መሠረተ ቢስ" ብለውታል። ኃላፊው "ህዳሴ ግድብ ከ20ዐ3 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሀብት፣ ጉልበት፣ እውቀትና በኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እየተገነባ ያለ ነው” ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል። አክለውም የአሜሪካው መሪ ንግግር ከዓለም አቀፋ ፖለቲካ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተናግረዋል። ከ15 ዓመት በፊት ለግንባታው መሰረት ድንጋይ ሲጣል 80 ቢሊዮን ብር ያስፈልገዋል ተብሎ የተጀመረው የታላቁ ህዳሴ…