Nileriver

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ስራዎች ብቻ ቀርተውታል ተባለ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ስራዎች ብቻ ቀርተውታል ተባለ

ከ13 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 95 በመቶ መድረሱን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባት ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ የግድቡ አጠቃላይ የሲቪል ስራው ግንባታ የደረሰበት ደረጃ 98 ነጥብ 9 በመቶ ተጠናቋል የተባለ ሲሆን የኤሌክትሮ መካኒካ ስራው ደውም በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን ከአፍሪካ ግዙፉ ፕሮጀክት የሆነው የህዳሴው ግድብ በአሁኑ ወቅት በሁለት ተርባይኖች 540 ሜጋ ዋት በማመንጨት ላይ ይገኛል፡፡ የጽህፈት ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ አብርሃም የግድቡ ግንባታ የተጀመረበትን 13ኛ ዓመት አስመልክቶ እንደተናገሩት አሁን ላይ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ እየተመረተ ያለው ኤሌትሪክ ኃይል በ2 ተርባይኖች 540 ሜጋ ዋት መሆኑን ያነሱ…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራ በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች እና ፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ከሁለት ወራት የእረፍት ጊዜ በኋላ ተከፍቷል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በምክር ቤቶቹ የመክፈቻ ንግግራቸው ላይ የመንግስትን የአንድ ዓመት የትኩረት መስኮች ይፋ አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ በንግግራቸው ላይ ያለፈው ዓመት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ግድብ 4ኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠረናቀቁ ትልቁ ስኬት ነበር ብለዋል፡፡ 90 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀው የህዳሴው ግድብ የሲቪል ምህንድስና ስራ ሙሉ ለሙሉ በዚህ ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል፡፡ ይህ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ የሚያመነጭ ግድብ ሳይሆን የቱሪዝምና የውሃ ሀብት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የሞራል ልዕልና ነው ብለዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም መንግስት በተያዘው ዓመት የሕግ የበላይነትን ማስከበር፣ የኑሮ ውድነትን መቀነስ፣ የስራ እድል ፈጠራ ፣ የምግብ ዋስትና እና መልካም አስተዳድር ልዩ ትኩረት…
Read More
የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የግድቡ አራተኛ እና ና የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው፤  ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። " በማለት የግድቡ የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በስራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል" ብለዋል። ከ12 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታው 91 በመቶ ደርሷል ተብሏብ። ኢትዮጵያዊያን በሚያዋጡት ገንዘብ እነ በመንግስት ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በ5ሺህ 200 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ ፕሮጀክት ነው። የህዳሴው…
Read More