27
Nov
አማራ ክልል ዉስጥ እየተደረገ ባለ ውጊያ ምክንያት ከ 7000 በላይ እስረኞች ከማረሚያ ቤት አምልጠዋል ተብሏል። ከአመለጡት መካከል አንዳንዶቹ በተጠቂዎች መገደላቸዉ ሲገለፅ ሌሎቹ ደግሞ ከሳሾቻቸዉ ላይ ጉዳት ማድረሳቸዉ ተነግሯል። የአማራ ክልል ምክር ቤት እንዳስታወቀው በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከአሥር ማረሚያ ቤቶች ሰባት ሺሕ ታራሚዎች መበተናቸውን ገልጿል፡፡ በምክር ቤቱ መደበኛ ጉባዔ ላይ እንደተገለጸው በክልሉ በወቅታዊ የፀጥታ ችግር ምክንያት ከተበተኑበት ተይዘው የተመለሱት በጣም አነስተኛ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ ባለው ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር ላይ የሚደረገው ቁጥጥር በታቀደው ልክ አለመሳካቱን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ በሚታየው የፀጥታ ችግር የሕዝቡ ነፃ እንቅስቃሴ በሰፊው የተገደበ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን ግድያ፣ ዝርፊያ፣ ዕገታ፣ የዜጎች እንግልት፣ ከእሴትና…