03
Sep
የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስትር ሀብታሙ ኢተፋ ከሪፖርተር መጽሄት ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ላይ እንዳሉት በታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት 15 ሺህ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ህይወታቸውን ካጡ ዜጎች መካከል የቀድሞው የግድቡ ግንባታ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ አንዱ ሲሆኑ ለብቻቸው መታሰቢያ ሀውልት እንደማይቆምላቸውም ሚንስትሩ ተናግረዋል። "የጸጥታ ሀይሎች፣ ሹፌሮች፣ ሰራተኞች እና ሌሎሽም የህብረተሰብ ክፍሎች ህይወታቸውን አጥተዋል ስለዚህ ይህ በሆነበት ሁኔታ ለግለሰቦች የተለየ መታሰቢያ ሀውልት የለም" ሲሉም ሚንስትሩ በቃለ መጠይቁ ወቅት ገልጸዋል። በግዝፈቱ ከአፍሪካ ቁጥር አንድ የሆነው የህዳሴው ግድብ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚመረቅ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሰሞኑ በኢትቪ በተላለፈ ንግግራቸው ለግድቡ ግንባታ አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል። የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትር…