Abayriver

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ስራዎች ብቻ ቀርተውታል ተባለ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሊጠናቀቅ ጥቂት ስራዎች ብቻ ቀርተውታል ተባለ

ከ13 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈፃፀም 95 በመቶ መድረሱን የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባት ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ የግድቡ አጠቃላይ የሲቪል ስራው ግንባታ የደረሰበት ደረጃ 98 ነጥብ 9 በመቶ ተጠናቋል የተባለ ሲሆን የኤሌክትሮ መካኒካ ስራው ደውም በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በሚያመነጨው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን ከአፍሪካ ግዙፉ ፕሮጀክት የሆነው የህዳሴው ግድብ በአሁኑ ወቅት በሁለት ተርባይኖች 540 ሜጋ ዋት በማመንጨት ላይ ይገኛል፡፡ የጽህፈት ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ አብርሃም የግድቡ ግንባታ የተጀመረበትን 13ኛ ዓመት አስመልክቶ እንደተናገሩት አሁን ላይ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ እየተመረተ ያለው ኤሌትሪክ ኃይል በ2 ተርባይኖች 540 ሜጋ ዋት መሆኑን ያነሱ…
Read More
የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

የታላቁ ህዳሴ ግድብ አምስት ተርባይኖች በቅርቡ ሀይል ማመንጨት እንደሚጀምሩ ተገለጸ

በ2016 በሕዳሴው ግድብ አምስት ተጨማሪ ዩኒቶችን ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን፤ የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አስታውቀዋል፡፡ የሕዳሴ ግድቡ አራተኛ ዙር የውኃ ሙሌት መጠናቀቁን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የሙሌቱ መጠናቀቅ በይፋ ተበስሯል፡፡ በሥፍራው ለተገኙ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ የሰጡት የታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ፤ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 93 በመቶ መጠናቀቁን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ግድቡ፤ ግራ፣ ቀኝ እና መካከለኛ አካል እንዳለው የተናገሩት ኢንጂነር ክፍሌ፤ ግራና ቀኙ የግድቡ ክፍል ከ635 እስከ 645 ደረጃ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የግራና ቀኙን ክፍል ለማጠናቀቅ ከዘጠኝ እስከ አሥር ሜትር ድረስ ብቻ እንደሚያስፈልግም አስታውቀዋል፡፡…
Read More
የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር የውሀ ሙሌት ተጠናቀቀ

የግድቡ አራተኛ እና ና የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ  "የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበስር በታላቅ ደስታ ነው፤  ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል። " በማለት የግድቡ የመጨረሻ ሙሌት መጠናቀቁን አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በስራው ውስጥ የተሳተፋችሁ ሁሉ  እንኳን ደስ አላችሁ፤ ይህ ኅብረታችን በሌሎች ጉዳዮቻችንም ሊደገም ይገባዋል" ብለዋል። ከ12 ዓመት በፊት የተጀመረው የታላቂ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ ግንባታው 91 በመቶ ደርሷል ተብሏብ። ኢትዮጵያዊያን በሚያዋጡት ገንዘብ እነ በመንግስት ወጪ እየተገነባ ያለው ይህ ግድብ በ5ሺህ 200 ሜጋ ዋት ሀይል በማመንጨት ከአፍሪካ ትልቁ ፕሮጀክት ነው። የህዳሴው…
Read More